ከደራሲያን ዓምባ

Monday, September 24, 2012

የግጥም ጥግ

እሳት ወይ አበባ 

ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን
እሳት ወይ አበባ

 ሌት ከዋክብቱ  እንደ ፀደይ
አጥለቅልቆን  በቀይ አደይ
ሰማዩ  ሥጋጃ  አጥልቆ
ተሽለምልሞ  አንጸባርቆ
ፈክቶ አሸብርቆ  ደምቆ
በአዝመራ  በአጥቢያ  ዐፀድ  ሰፍኖ
የዓደይ  አዝርዕት  ተከሽኖ
በዕንቁጣጣሽ  ሰብል  ታጥኖ
ኢዮሃ  አበባዬ  ሆኖ፥
ጨረቃዋ  ከቆባዋ፥  ከሽልምልሚት  እምቡጧ
ብላ ከሰንኮፈንዋ፥ ተንዠርግጎ የእንኮይ ቡጧ፥
ድንግል  ጽጌ-ረዳ  ፈልቃ
ፍልቅልቂት  ድምቡል ቦቃ
ተንሠራፍታ  የአበባ  ጮርቃ፥
ታድያን  ብሌኑ  የጠጠረ
ባሕረ-ሃሳቡ የከረረ
የውበት ዓይኑ የታወረ
ልበ-ሕሊናው  የሰለለ
አይ፥ አበባ አይደለም አለ፤
አይ፥ እሳት አይደለም አለ፤
ያልታደለ።
ሰማይ  ጨለማ  ነው እንጂ፥  እሳት አደል ብሎ ካደ
እቶን  ባይኑ  እየነደደ።
ከዋክብቱ  እንደ  ችቦ
በነበልባል  ወርቀ  ዘቦ
ከፅንፍ  ፅንፍ  አውለብልቦ
ደመራው  እየተመመ
እየፋመ  እየጋመ
ደመና  እንደንዳድ  ሲነድ
መንጸባርቅ  ሰደድ  ሲወርድ፥
በራሪ  ኮከብ  ተኩሶ
በአድማሳት  እሳት  ለኩሶ
ይኸ እንደኔና  እንዳንቺው፥  የውበት ዓይኑ  የሰለለ
ሰማይ ጨለማ ነው እንጂ፥  እሳት እኮ አይደለም አለ፥
ያልታደለ።

ይቅር ብቻ  አንናገርም፥
እኔና  አንቺ  አንወያይም፤
ለውይይት  አልታደልንም
እንዲያው ዝም፥ እንዲያው ዝምዝም።
አበባ አንሆን ወይ እሳት
ተጠምደን  በምኞት  ቅጣት
ሰመመን  ባጫረው  መዓት
ዕድሜ አችንን እንዳማጥናት፤

እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ  እንቅ  ስንባባ
ባከነች  ልጅነታችን፥ እየቃተትን ስናነባ
ሳንፈጠር  በሞትንባት
ሳናብብ  በረገፍንባት
ሳንጠና ባረጀንባት
አበባ ወይንም እሳት፥  መሆኑን ብቻ አጣንባት።
*************************************************
1966 ዓ.ም.
ብርሀንና ሠላም ማተሚያ ቤት

 

 

ከመጽሃፍት ገፆች

ደራስያን በተለያዩ ዘመናትና ሁኔታዎች ውስጥ ያጋጠማቸውን የማኅበረሰቡን የሮሮም ሆነ የፍስሐ መንፈስ በመገምገምና አስመስለው በመቅረጽ ሥነ ቃልን ይጠቀማሉ፡፡ ለመልዕክቶቻቸው ማጉያ በማድረግ በሚፈጥሯቸው ገፀ ባሕርያት አማካይነት በልዩ ልዩ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻቸው ውስጥ ሲጠቅሷቸውም እናስተውላለን፡፡


"እግዚአብሔር ሲፈጥረኝ ጥንቱን በዚህ መሬት፣
ሳለቅስ ተወልጄ ሳለቅስ ኖሬበት፣
ሳለቅስ እንድሔድ ወደ ማልቀርበት፣
መከራን ጠግቤ ደስታን ምራብበት፣
ሌሎች የበሉትን እዳ ልከፍልበት፡፡ "


(ከ ፍቅር እስከ መቃብር)

Wednesday, September 19, 2012

የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር

በዘመነ ኢህአዲግ













የዜግነት ክብር በኢትዮጵያችን ፀንቶ
ታየ ህዝባዊነት ዳር እስከዳር በርቶ
ለሰላም ለፍትህ ለህዝቦች ነፃነት
በእኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት
መሰረተ ፅኑ ሰብዕናን ያልሻርን
ህዝቦች ነን ለስራ በስራ የኖርን
ድንቅ የባህል መድረክ ያኩሪ ቅርስ ባለቤት
የተፈጥሮ ፀጋ የጀግና ህዝብ እናት
እንጠብቅሻለን አለብን አደራ
ኢትዮጵያችን ኑሪ እኛም ባንቺ እንኩራ።
*****************************
በ1984 ዓ.ም
ግጥም፦-ደረጀ መላኩ መንገሻ፤
ዜማ፦- ሰሎሞን ሉሉ ምትኩ

*********************
*********************

በዘመነ ደርግ



















ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -ኢትዮጵያ ቅደሚ
በኅብረተሰባዊነት - አብቢ ለምልሚ!
ቃል ኪዳን ገብተዋል - ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ - ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት - ለነፃነትሽ
መስዋዕት ሊሆኑ - ለክብር ለዝናሽ!
ተራመጂ ወደፊት - በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለሥራ - ላገር ብልጽግና!
የጀግኖች እናት ነሽ -  በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ - ለዘላለም ኑሪ።
*************************
በ1968 ዓ.ም 
ግጥም፦-በአሰፋ ገብረማርያም
ዜማ፦-አቶ ዳንኤል ዮሐንስ

*********************
*********************

በንጉሱ ዘመን


ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ
በአምላክሽ ኃይል በንጉስሽ
ተባብረዋልና አርበኞችሽ
አይነካም ከቶ ነፃነትሽ
ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ
አትፈሪም ከጠላቶችሽ።
ድል አድራጊው ንጉሣችን
ይኑርልን ለክብራችን።
****************
በ1919 ዓ.ም
ግጥም፦-በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
ዜማ፦-ኬቨርክ ናልባልድያን

********************

ኢትዮጵያ



ኢትዮጵያ ~ Ethiopia  /aityoP'ya/


ኢትዮጵያ የሚለው ስያሜ መሠረቱ ግሪክ ሲሆን ከክርስቶስ ልደት በፊት በውል ከታወቀችው ከግብፅ በስተደቡብ የሚገኘው የአፍሪቃ ክፍልና ደቡብ ምዕራብ እስያ የሚጠሩበት አጠቃላይ ስም ነበር፡፡ ይሁንና ከክርስቶስ ልደት በኋላ አገባቡ ጠበብ እያለ አሁን ኢትዮጵያ የምትገኝበት አካባቢ መጠሪያ ለመሆን በቃ፡፡ ስያሜውን ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ በጠበበና እስካሁንም ቋሚ በሆነ መልኩ የምናገኘው
በ4ኛው ምእተ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የክርስትናን እምነት የተቀበለው የአክሱም ንጉሥ ዔዛና በድንጋይ ላይ ባስቀረፀው አንድ ጽሑፍ ላይ ራሱን የኢትዮጵያ ንጉሥ ብሎ ሲጠራ ነው፡፡ ከዚያም በተከታታዮቹ ምእተ ዓመታት በጊዜው በተጻፉ ጽሑፎች አክሱም የኢትዮጵያውያን ከተማ፣ አፄ ካሌብ ደግሞ የኢትዮጵያውያንንጉሥ ተብለው ሲጠቀሱ ስናይ ስያሜው ቋሚ መልኩን እየያዘ መምጣቱን እንረዳለን፡፡ በ14ኛው ምእት ዓመት መጀመሪያ ላይ የተጻፈው ክብረ ነገሥት የተሰኘው ንግሥተ ሳባ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ያደረገችውን ጉዞ የሚያትተው መጽሐፍም፣ ኢትዮጵያ የሚለው ስያሜ በአሁኒቱ ኢትዮጵያ ካለችበት ግዛት ጋር ያለውን መያያዝ ኦፊሲዬል አድርጎታል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ነገሥታት መደበኛ መጠሪያቸውም "ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ወይም "ንጉሠ ኢትዮጵያ" ሆኖ ቆይቷል፡፡
 
 

ስለ ኢትዮጵያ ዕይታ

ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ የአፍሪካ ቀንድ በመባል በሚታወቀው አካባቢ የምትገኝ ከአፍሪካ በቆዳ ስፋቷ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ የምትገኘ አገር ናት፡፡ ዙሪያዋን አምስት አገሮች ያዋስኗታል፡፡ በምስራቅ በኩል ጅቡቲና ሶማሊያ፤ በሰሜንና በሰሜን ምስራቅ ኤርትራ፤ በደቡብ ኬንያ እና በምእራብ ሱዳን ናቸው፡፡ ጠቅላላ የቆዳ ሰፋት 1.1 ሚሊዬን ካሬ ሲሆን በውስጧ 7000 ኪ.ሜ የሚደርስ ርዝማኔ ያላቸው አስር ትላልቅ ወንዞችና ወደ 7000 ካሬ ጠቅላላ ስፋት ያላቸው ሀይቆች አሏት፡፡
መልክአ ምድር
ኢትዮጵያ በውስጧ የተለያዩ መልክአ ምድር ያላት አገር ከመሆኗ በተጨማሪ የአየር ንብረት አፈር የእንስሳትና የዕፅዋት ስብጥር የሚስተዋልባት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ በጣም ከፍተኛ የሆኑ ተራሮች ከላያቸው ጠፍጣፋ የሆኑ አምባ የሚባሉ ኘላቶዎች ስምጥ የሆኑ ሸለቆዎች፤ ጥልቅ የወንዝ ሸለቆዎችና ሰፋፊ ሜዳዎች በውስጧ ይዛለች፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 4620 ሜትር ከሚደርሰው ዳሽን ተራራ እስከ 148 ሜትር ከባህር ጠለል በታች እስከሆነው የዳሎል ዲኘረሽን ድረስ የሚሆን ልዩነት ያለው የከፍታና ዝቅታን የምታስተናግድ አገር ናት፡፡
ለም ከሆኑ መሬቶችና ተራሮች ምንም የማይታይባቸው ከሚመስሉ መሬቶች አንስቶ፣ ኢትዮጵያ በብዙ ገባሮችና ትላልቅ እንደ አባይ ተከዜ አዋሽ ኦሞ ዋቢ ሸበሌና ባሮ-አካቦ በመሳሰሉ ወንዞች የታደለች አገር ናት፡፡
ከሜዲትራንያን ምስራቃዊ መጨረሻ ተነስቶ፣ ደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው ሞዛንቢክ ድረስ የሚደርሰው ታላቁ የስምጥ ሸለቆ ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍሏት ያልፋል፡፡
የአየር ንብረት
ኢትዮጵያ እንደ መልክአ ምድራዊ አቀማመጧ የአየር ንብረቷም በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ሁኔታ ይታዩባታል፡፡ የመካከለኛው ኘላቶ አካባቢ ብዙም የማይፈራረቅ አይነት ወይናደጋማ አይነት የአየር ንብረት ይታይበታል፡፡ ዝቅተኛው የአየር ንብረት በአማካኝ 60c ሲሆን ነገር ግን ወደ ቀይባህር በረሀ አካባቢ 600c የሚደርስበት ጊዜዎች አሉ፡፡ በብዙ የአገሪቱ አካባቢ በክረምት ወራት ይኸውም ሰኔ ሀምሌና ነሀሴ ውስጥ ከፍተኛ የዝናብ መጠን ይመዘገባል፡፡ 
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር
የኢትዮጵያ (እንዲሁም በኤርትራ አብያተ ክርስትያናት) ዋና ካሌንደር ነው። አዲስ ዓመት በጁሊያን ካሌንደር አቆጣጠር በኦገስት 29 ወይም 30 የሚጀምር ሲሆን በግሪጎሪያን ካሌንደር ደግሞ 1901 ... እስከ 2099 ... ድረስ በሴፕቴምበር 11 ወይም 12 ይጀምራል። በየአራት ዓመቱ አንድ ቀን ይጨመራል። በአንድ ዓመት ውስጥ አስራ-ሁለት ባለሠላሣ ቀናት እና አንድ ባለ አምስት (ስድስት በአራት ዓመት አንዴ) ቀናት ያሉባቸው ወራት አሉ።
የአመተ ምህረት ዘመናት ከጎርጎርዮስ 'አኖ ዶሚኒ' 7 ወይም 8 አመታት የሚለይበት ምክንያት፣ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 400 አመት ያህል በኋላ አኒያኖስ እስክንድራዊ ዘመኑን ሲቆጥረው ትስብዕቱ በመጋቢት 29 1 .. እንደ ሆነ ስለ ገመተ ይህ ትስብዕት ዘመን 1 አመት ሆኗል። ይህ አቆጣጠር በምሥራቅ ክርስቲያን አገራት ከተቀበለ በኋላም 443 .. ከሮማ ፓፓና ከምሥራቅ አቡናዎች መካከል ልዩነት ደርሶባቸው፤ 517 ሌላ መነኩሴ ዲዮኒሲዮስ ኤክሲጉዎስ ሌላ አቆጣጠር (አኖ ዶሚኒ) አቀረበ። በሱ ግምት ትስብዕቱ የተከሠተበት ቀን ከአኒያኖስ ግምት በፊት 8 አመታት አስቀደመው። አኖ ዶሚኒ አቆጣጠር በምዕራብ አውሮፓ ላይኛነት በማግኘቱ የትስብእት ዘመን 1 አመተ ምህረት አኖ ዶሚኒ 9 .. ሆነ።
የኢትዮጵያ ዘመን ኣቆጣጠር የጁልያን ዘመን ኣቆጣጠር ኣይደለም።
ወራት
የወራት አቆጣጠር የተወረሰ ቅብጢ ዘመን አቆጣጠር ይህም የወጣ ጥንታዊ ግብጽ ዘመን አቆጣጠር ነው። ሆኖም የወሮች ስሞች ግዕዝ ተለውጠዋል።

ቋንቋ
አራት መሰረታዊ የቋንቋ ቤተሰቦች ሲኖር እነርሱም ኩሺቲክ (Cushitic) ፣ ሴሜቲክ (Sematic) ፣ ኦሜቲክ (Omotic) ፣ ኒሎ ሻሮን (Nilo-Saharan) በመባል ይታወቃሉ።
በግምት 83 የተለያዩ ቋንቋዎችና ከ200 የሚበልጡ የአነጋገር ዘዬዎች በአገሪቱ ይነገራሉ።
አማርኛ የብሄራዊ ቋንቋ ሲሆን የንግድና የስራ መግባብያ ቋንቋዎች አማርኛ እና እንግሊዝኛ ናቸው።
መልክአ ምድር
ኢትዮጵያ በውስጧ የተለያዩ መልክአ ምድር ያላት አገር ከመሆኗ በተጨማሪ የአየር ንብረት አፈር የእንስሳትና የዕፅዋት ስብጥር የሚስተዋልባት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ በጣም ከፍተኛ የሆኑ ተራሮች ከላያቸው ጠፍጣፋ የሆኑ አምባ የሚባሉ ኘላቶዎች ስምጥ የሆኑ ሸለቆዎች፤ ጥልቅ የወንዝ ሸለቆዎችና ሰፋፊ ሜዳዎች በውስጧ ይዛለች፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 4620 ሜትር ከሚደርሰው ዳሽን ተራራ እስከ 148 ሜትር ከባህር ጠለል በታች እስከሆነው የዳሎል ዲኘረሽን ድረስ የሚሆን ልዩነት ያለው የከፍታና ዝቅታን የምታስተናግድ አገር ናት፡፡
ለም ከሆኑ መሬቶችና ተራሮች ምንም የማይታይባቸው ከሚመስሉ መሬቶች አንስቶ፣ ኢትዮጵያ በብዙ ገባሮችና ትላልቅ እንደ አባይ ተከዜ አዋሽ ኦሞ ዋቢ ሸበሌና ባሮ-አካቦ በመሳሰሉ ወንዞች የታደለች አገር ናት፡፡
ከሜዲትራንያን ምስራቃዊ መጨረሻ ተነስቶ፣ ደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው ሞዛንቢክ ድረስ የሚደርሰው ታላቁ የስምጥ ሸለቆ ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍሏት ያልፋል፡፡
የአየር ንብረት
ኢትዮጵያ እንደ መልክአ ምድራዊ አቀማመጧ የአየር ንብረቷም በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ሁኔታ ይታዩባታል፡፡ የመካከለኛው ኘላቶ አካባቢ ብዙም የማይፈራረቅ አይነት ወይናደጋማ አይነት የአየር ንብረት ይታይበታል፡፡ ዝቅተኛው የአየር ንብረት በአማካኝ 60c ሲሆን ነገር ግን ወደ ቀይባህር በረሀ አካባቢ 600c የሚደርስበት ጊዜዎች አሉ፡፡ በብዙ የአገሪቱ አካባቢ በክረምት ወራት ይኸውም ሰኔ ሀምሌና ነሀሴ ውስጥ ከፍተኛ የዝናብ መጠን ይመዘገባል፡፡
በከፍታና በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዐይነት የአየር-ንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነሱም:-
  • ደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግረ ሴ.ግ የማይበልጥ፤
  • ወይናደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል ከ1500 እስከ 2400 ሜትር፣ ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስና፣
  • ቆላ - ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስ አከባቢዎች ናቸው።
ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።
*********************************************************************************
ምንጭ:--http://am.wikipedia.org/// http://www.ethiopia.gov.et