ከደራሲያን ዓምባ

Tuesday, October 23, 2018

ፀሐፊ ተውኔት ኃይሉ ፀጋዬ _በሸገር መዝናኛ

ሰብአዊ ስሜት ….የህሊና ‘ረፍት!_ኬቨን ካርተር


በፈረንጆቹ አቆጣጠር ማርች 1993 ‹‹ኬቨን ካርተር›› የተባለ ደቡብ አፍሪቃዊ የፎቶ ግራፍ ባለሙያ ሱዳን ውስጥ ተከስቶ በነበረው ችጋር የተነሳ ከተባበሩት መንግስታት የእርዳታ ልኡክ ጋር ለደግነት በደቡብ ሱዳን ከተመ፡፡ በአንዱ መከረኛ እለትም ይህቺን ከታች የምትመለከቷትን ምስል በካሜራው አስቀረ፡፡
‹‹ርሀብ አድቅቆት የገዛ ራሱን መሸከም ያቃተው ህፃን ልጅ ‹‹……….እና ……..››ይህን ገላ ለመግመጥ የቋመጠ ጥንብ አንሳ››
የረሀብን ክፉ ገፅታ ….የድርቅን አሰቃቂ ሁነት….የምስኪኖችን እልቂት ….ቃላት ሊገልፁ ከሚችሉበት አቅም በላይ በሆነ መንገድ በድንቅ ካሜራው ለአለም አስቃኘ፡፡
‹‹ቀጫጫ እጆች…..እንኳን ለመሮጥ፣ለመቦረቅ ይቅርና የገዛ አካሉን ለመሸከም ያዳገተው እግር፣ መቆም የከበደው ገላ‹‹….. እና …….››ፈርጣማ አሞራ!!››


 ይህ ፎቶ እንደ እ.ኤ.አ በማረች 26 1993 ለኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ተሸጦ ታተመ፡፡ ምስሉ በመላው አለም ታየ፣ ክብር እና ዝናን አተረፈ፡፡ የባለሙያው ስም….ከፍ ከፍፍፍፍፍፍፍ…. አለ፡፡ተሸለመ፣ተሞገሰ፣ተከበረ፡፡
ከዚህ ሽልማት በውሀላ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከአንድ ጥግ የተወረወረች ያልተጠበቀች ጥያቄ ግን የህይወቱን አቅጣጫ እስከወዲያኛው ቀየረችው፡፡አመሳቀለችው፡፡
‹‹ህፃኗ ልጅ እንዴት ሆነች….ታደግካት?????????>>
አይኖቹ ፈጠጡ….ላብ አጠመቀው………ቃላት ከአንደበቱ ጠፋ!!………..በሀሳብ ጥቂት ወደ ደቡብ ሱዳንዋ መንደር ተሰደደ፡፡ጠያቂው ግን ድጋሚ በጩኸት ጠየቀ
‹‹ህፃንዋን ልጅ ታደግካት ወይ????››
ካርተር ጋዜጣዊ መግለጫውን አቋርጦ ወጣ፡፡ ከወዳጅ ከዘመድ ሁሉ ተሰወረ፡፡ በብቸኝነት ገዳም ውስጥ….በፀፀት ተከተተ፡፡



በገዳይዋ ፊት ጥሏት የሄደው ጎስቋላ ህፃን ነፍስ ለወራት እንቅልፍ ነሳው፡፡የፎቶግራፍ ሽልማቱን ባሸነፈ በሶስት ወሩ በልጅነቱ ሲቦርቅ ባደገባት ‹‹ፓርክሞር›› በተባለች ለምለም ቀዬ በ33 አመቱ እራሱን ገድሎ ተገኘ፡፡
በሞቱ ዋዜማ ላይ ሆኖ ለወዳጅ ዘመዶቹ ባስቀረው ማስታወሻ የሚከተለውን ፀፀት አሰፈረ
.
“I’m really, really sorry. The pain of life overrides the joy to the point that joy does not exist… depressed … without phone … money for rent … money for child support … money for debts … money!!! … I am haunted by the vivid memories of killings and corpses and anger and pain … of starving or wounded children, of trigger-happy madmen, often police, of killer executioners … I have gone to join Ken if I am that lucky.”
ስንደመድም፡-
ከምንም ከምንም ነገር በፊት ሰብአዊ ስሜት!!! ክብር ፣ሽልማት፣ አዱኛ………ከሰውነት ወዲያ ይደርሳል!!!! /////////////////////////////////////////////////////********************///////////////////////////////////////////////////
ምንጭ:- http://getutemesgen24.com/
              http://100photos.time.com/photos/kevin-carter-starving-child-vulture