ከደራሲያን ዓምባ

Monday, October 22, 2012

ከደራሲያን ዓምባ

ከበደ ሚካኤል


ከበደ ሚካኤል (1909-1991)
በደብረ ብርሃን ከተማ፣ ገርም ገብርኤል አጥቢያ ጥቅምት 23 ቀን 1909 ዓ.ም.ተወለዱ። ወደ አዲስ አበባ እንደ መጡ መጀመሪያ በአሊአንስ ኢቲዮ-ፍራንሴዝ በኋላም በላዛሪስት ሚሲዮን ትምህርታቸውን ተከታተሉ። የሼክስፒርን ሮሜዎና ዡልየትን ማክቤዝን በመተርጎም እውቅናን ለማትረፍ ችለዋል።
ከበደ ሚካኤል 30 ገደማ መፃሕፍትን ፅፈዋል።
ከበደ ሚካኤል በርካታ የስነ ጽሁፍ ስራዎች ባለቤት በመሆናቸው በተለይም ለልጆች ትምህርት አዘል ጽሁፎችን የግጥም የፈጠራ ስራዎችን ቅኔዎችን በስፋት በማበርክታቸው በኢትዮጵያ የስነጽሁፍ መድረክ ገናና ከሆኑት ደራሲዎች አንዱ ናቸው። 
የሰዎች ስነ ምግባር ላይ የማተኮርና ምክር አዘል መልእክቶችን የማስተላለፍ ዝንባሌአቸው በአብዛኛው ስራቸው ላይ ይንጸባረቃል።
ዘመናዊት ኢትዮጵያን ለማደርጀት በተደረገው ትግል በግንባር ቀደምትነት የተሳተፉ እኒህ ፈላስማ፥ ባለቅኔ፥ ጸሐፌ-ተውኔት፥ ደራሲና አንጋፋ ጋዜጠኛ ፥ የቀለም ሰው በሀገራችን የመጀመሪያ የነበረውን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሽልማት ድርጅት በቀዳሚነት የተቀበሉ ሲሆን፣ አዲስ ትውልድ ላፈራ ስብእናቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 26 ቀን 1990 ዓ.ም. በሥነ ጽሑፍ የክብር ዶክቶሬት ዲግሪ ሸልሟቸዋል። በተረፈም ከፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ሶቭየት ህብረትና ሜክሲኮ ሽልማትን ተቀብለዋል።
በተረፈ የትምህርት ሚኒስትር ዳይረክተር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተከታይ ዳይሬክተር (1942)፣ የብሄራዊ መጻህፍት ቤት ዳይረክተር (1944)ና የካቢኔ ሚንስትር ሆነው አገልግለዋል።
ክቡር ዶክቶር ከበደ ሚካኤል፥ ኢትዮጵያዊ የቀለም ሰው ኅዳር 3 ቀን 1991 ዓ.ም. በሰማንያ ሁለት ዓመታቸው አረፉ።


የ ክቡር ዶክቶር ከበደ ሚካኤል ሥራዎች:--

  1. የትንቢት ቀጠሮ (ሥነ-ግጥም መማሪያ መጽሀፍ) 1938
  2. ሮሚዎና ዡሊየት (ተውኔት ትርጉም) 1946
  3. ታላላቅ ሰዎች (ኢ-ልብወለድ) 1943
  4. የዓለም ታሪክ (ኢ-ልብወለድ) 1956
  5. አኒባል (ተውኔት-ግጥም) 1956
  6. የቅጣት ማዕበል (ተውኔት-ግጥም) 1951
  7. ሄሮዶተስ (ኢ-ልብወለድ-ትርጉም)
  8. ታሪክናምሳሌ (መማሪያ መጽሀፍ) 1934
  9. ጃፓን እንዴት ሰለጠነች (ኢ-ልብወለድ) 1946
  10. የዕውቀት ብልጭታ (ኢ-ልብወለድ) 1939
  11. ካሌብ (ተውኔት) 1958
  12. ኢትዮጵያና ምዕራባዊ ስልጣኔ (ኢ-ልብወለድ) 1941
  13. የኀሊና ደወል
  14. ብርሃንና ኅሊና (ሥነ-ግጥም) 1933
  15. የኢትዮጵያ የጥንት ዕሎች 1961
  16. አክአብ (ተውኔት)
  17. ሥልጣኔ ምንድነች? (ኢ-ልብወለድ)
  18. የቅኔ ውበት (ሥነ-ግጥም) 1957

ከግጥሞቻቸው በጥቂቱ :--

የተማረ ሆኖ እውነቱን የማይገልጽ ፣ 
ባለ ጸጋ ሆኖ ገንዘቡን የማይሰጥ፣
ደሃ ሆኖ መስራት የማይሻ ልቡ፣
ሶስቱም ፍሬ ቢሶች፣
ለምንም አይረቡ።
*************
ፍሬ መሬት ወድቆ ከዋለ ካደረ፣
ሠው ገንዘብ አግኝቶ መክበር ከጀመረ፣
የመጣ ነውና ቀድሞውንም ከጥንት፣
ሁለቱም አይድኑም ከመበላሽት
        **********************
ጊዜ እየበረረ ሳይታጠፍ ክንፉ፣
እኛ በቁማችን ምንድነው እንቅልፉ።

**************************

መርዝም መድሃኒት ነው ሲሆን በጠብታ፣
እንዲሁም ለተንኮል አለው ቦታ ቦታ፣
ምን ቢሰለጥኑ ቢራቀቁ በጣም፣
ሁልጊዜ ደጋግሞ ብልጠት አያዋጣም።
በጅ የተበተቡት ተንኮል ዞሮ ዞሮ፣
ማጋለጡ አይቀር እጅና እግር አስሮ ።
መጽሓፉም ይለናል ሲያስተምረን ጥበብ፣
ብልጥ ሁን እንደባብ የዋህ ሁን እንደርግብ፣
ስለዚህ በብልጠት ተንኮል ስትሰሩ፣
በዝቶ እንዳይገላችሁ ገርነት ጨምሩ

Friday, October 5, 2012

ምርጥ አባባሎች

''' ምርጥ አባባሎች'''


• በአንድ ሰው የማስታወሻ መያዣ ደብተር ውስጥ ቦታ ማግኘት ይቻላል፡፡ ነገር ግን በልቡ ውስጥ ቦታ ማግኘት ችግር ነው፡፡
• ሕጎችን ማውጣት ቀላል ነው መተግበር ግን ችግር ነው፡፡
• በየዕለቱ ማለም ቀላል ነው፡፡ ህልምን እውን ለማድረግ መታገል ግን ከባድ ነው፡፡
• ሙሉ ጨረቃን አይቶ ማድነቅ ቀላል ነው፡፡ የጨረቃን ሌላ ገጽታ ማየት ግን ችግር ነው፡፡
• ለአንድ ሰው አንድ ቃል መግባት ይቻላል፡፡ ቃልን መፈጸም ግን ችግር ነው፡፡
• ሌሎችን መውቀስ ይቀላል፡፡ ራስን ግን ይከብዳል፡፡
• አንድን ነገር ለማሻሻል ማሰብ ቀላል ነው፡፡ ማሰብን አቁሞ ወደ ተግባር መግባት ግን ጭንቅ ነው፡፡
• ሌሎችን በመጥፎነት መፈረጅ ቀላል ነው፡፡ ጥሩ ሊሆኑ ይችላሉ ብሎ ማሰብ ግን ከባድ ነው፡፡
• ፍቅር የሚጠይቀው ብቸኛ ስጦታ "ፍቅር" ነው፡፡ (ጆን ግሬይ)
• መሳሳት ሰብዓዊነት ሲሆን ስህተትን ማመን ግን ቅዱስነት ነው፡፡ (ዳፍ ባውርሰን)
• በሕዝብ ዘንድ አመኔታ ያለው ሰው ራሱን እንደ ሕዝብ ንብረት አድርጎ ይቆጥራል፡፡ (ቶማስ ጀፈርሰን)
• ወንዶች ሴቶችን የሚያፈቅሩትን ያህል ሰማያዊውን ዓለም ቢያፈቅሩ ኖሮ መላዕክት (አማልክት) መሆን በቻሉ ነበር፡፡ (ማልኮላም ኤክስ)

******************
ምንጭ:---(ምርጥነህ ታምራት፣ ጣዝማ፣ 1999)

-   የራስህ ቤተ መንግሥት ሁን፡፡ አለበለዚያ ዓለም እስር ቤትህ ትሆናለች፡፡ (ጀንደን)
-  ቅናት ሲመገብ ያደገ ፍቅር አሟሟቱ ከባድ ነው፡፡ (ዴቪድ)
-  ቅናትን እንደሳቅ የሚያስፈራው ነገር የለም፡፡ (ፍራንሷ ሳንጋ)
-  ቅናትን የሚፈጥረው ፍቅር ሳይሆን ራስ ወዳድነት ነው (ዋሊንግተን)
-  ከሞትክ አይቀር ደስ ብሎህ ሙት፡፡ (ቻርልስ ጀምስ ፊክስ)
-  ትዳር ያዙ ወይ የሞቀ ትዳር ይሆንላችሁና በደስታ ትኖራላችሁ፣ ወይም ጨቅጫቃ ትዳር ይሆንባችሁና ፈላስፋ ትሆናላችሁ፡፡ (ሶቅራጥስ)
-  ገበታህን በፍቅር ቅመም አሳምረው፡፡ ሁሉንም ሰሃን በደስታ ይሞላዋልና፡፡ (ዥን ኮክቶ)

***************************************************************

ምንጭ:---(ምርጥነህ ታምራት፤ጣዝማ የሚሊኒየሙ ምርጥ አባባሎች፣2000)

- የማያውቅ ማወቅንም የሚያውቅ ምሁር ነውና ተከተለው
- ለገዛ ራስህ ክቡር ዓላማዎች ታምኝ ሁን።
- የትምህርት ሁሉ ዓላማና ግብ ስብዕናን ማዳበር ነው።
- ማለዳ ስንነሳ ልብ እንበል? ከሐብት ሁሉ የሚልቁት 24 ሳዓታት የኛ ናቸው።
- ምንም ሳንሰራ ከምናሳልፈው ህይወት ስህተት እየሰራን የምንገፋው ህይወት የተሻለ ነው።
- የያውን ሁሉ ለመያዝ የሚሞክር አንድ ቀን እባብ ጨብጦ ይነደፋል።
- የቁም ነገር ጫፍ የሚባለው ሩቅ ያለውን መመልከት ሳይሆን በእጁ ያለውን መስራት ነው።-
- ስህተቱን ሲያውቅ ጩቤ የማይረግጥ ምሁር ምሁር ሊባል አይችልም።
- ነፃነት ስህተት የመሥራት መብትን ካላካተተ መኖር ፋይዳ የለውም።
- ሲጋራ በአካል ውስጥ የሚጓዝ የጫካ ውስት እሳት ነው።
- በዓለም ከፍተኛ መራራ ነገር ቢኖር ራዕይ አባል ሆኖ መፈጠር ነው።
- ባልና ሚስት በጋራ የሚተነፍስ ሳንባ ባይነራቸውም በጋራ የሚጓዝ የትዳር ሰንሰለት አላቸው።
- በዓለም ትልቁ ውርደት ከመስራት የሰው እጅ ማየት ነው።
- በአንድ ዛፍ የሚዘሉ ጉሬዛና ጦጣ አብረው ቢውሉም ተቃቅፈው አይተኙም።
- በኢላማህ የማትተማመን ከሆንክ ወደ ነብር አትተኩስ።
- በዛሬ ደስታ ብቻ የሚፈነድቁ ሰዎች ውብ አበባ ከተቀጠፈ መጠውለጉን የሚዘነጉ ናቸው።
- በፍቅር የተነሳ ልብ በፍቅር ይሰክናል።
- ብርቱካን መጨመቁን ቢያውቅ ውሃ አይዝልም ነበር።
- ብቃት የሚመጣው በውጥረት ሳይሆን በተግባር ምጥቀት ነው።
- ለማመን እንጂ ላለማመን ምክንያት አያስፈልግም::
- መልከመልካም ሴት ባየህ ጊዜ ተፈጥሮን አድንቅ እንጂ የዝሙትን መንፈስ አይሰማህ' ዝሙት ከደካማ መንፈስ የሚመንጭ ነው።
- እያንዳንዱ ይሕይወት ቀን ወደ ሞት የሚያደርስ ደረጃ ነው።
- ወደ ፊት የምንራመድ ከሆነ ታሪክን መድገም ብቻ ሳይሆን አዲስ ታሪክ መፍጠር አለብን።/መሀተመ ጋንዲ/ 

******************************************************************************
ምንጭ:---http://girmayreda.blogspot.com

Monday, October 1, 2012

ከደራሲያን ዓምባ

  ሀዲስ ዓለማየሁ እና ስራዎቻቸው 

                ( ጥቅምት 7 ቀን 1902 ዓ.ም- ህዳር 26 ቀን1996 ዓ.ም)

ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዶዳም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በ ጥቅምት ፯ ቀን ፲፱፻፪ ዓ.ም. ተወለዱ። 
ሀዲስ ዓለማየሁ በርካታ የስነጽሑፍ ሥራዋችን አበርክተዋል። 
  1. ተረት ተረት የመሰረት -1948 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  2. ኢትዮጵያ ምን ዓይነት አስተዳደር ያስፈልጋታል? - 1953 ዓ.ም. ((ኢ-ልብ ወለድ))
  3. ፍቅር አስክ መቃብር - 1958 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  4. ወንጀለኛው ዳኛ - 1974 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  5. የልም  ዣት - 1984 ዓ.ም.(ልብ ወለድ)
  6. የትምህርትና የተማሪ ቤት ትርጉም - 1948 ዓ.ም. (ኢ-ልብ ወለድ)
  7. ትዝታ - 1985 ዓ.ም. (ግለታሪክ )
  8. የአበሻና የወደኋላ ጋብቻ -  (ተውኔት)

 ሀዲስ ዓለማየሁ በኢትዮጵያ የስነ ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከታቸው 
በሥነ ጽሑፍ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሽልማት ድርጅት ተሸላሚ ፣
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክቶርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል ። 
ደራሲው በኅዳር 26 ቀን 1996 ዓ.ም. በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ።


 ምርጥ አባባሎች:-
  • " የትልቅ ሰውን ትልቅ ስራ ሌሎች ይናገሩለታል እንጂ እርሱ አይናገርም።" (የልም  ዣት)
  • " የምትወደው ሁልጊዜ ሲለይህ የሚያስረሳህ እንጂ የሚያስታውስህ  ነገር አትፈልግ ያለዚያ ህይወትህ የስቃይ ህይወት ይሆናል።" (ፍቅር አስክ መቃብር)
  • " ሰው ባለመብት የሚያደርገው የሚፈፅመው ተግባር ነው ተግባሩን ሳይፈጸም በመብቱ የተጠቀመ ሁሉ ባለዕዳ ነው።" (ወንጀለኛው ዳኛ)