ከደራሲያን ዓምባ

Monday, June 27, 2022

ጎዳናው ይገርማል?! ___በረከት በላይነህ



ጎዳናው ይገርማል?!

በረከት በላይነህ _ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ
************************
ይገርማል መንገዱ
እግረኛው ይገርማል

ሸራ ጫማ ባ'ይነት
በነጫጭ ካልሲ
በሲኪኒ ሱሪ
ከመምህሩ ጋራ
አይስክሬም ሚልስ
የሀይስኩል ተማሪ
.
ፀባይኛ ወጣት
ጃንቦ ተከልሎ
በምርቃና ሆኖ
ሀሳብ የሚፈትል
አንዲት ሙ......ደኛ እናት
በ'ድሜ ከልጆቼ አንሳለው የምትል
ፒዛውን የሚገምጥ
ጭማቂ የሚመጥ
አራዳ አባወራ
በሚስቱ ትከሻ
በልጆቹ ምላስ
ቅምጥ የሚጣራ
.
አንድ ፍሬ ሴቶች
በተገዛ ቅንድብ
በተገዛ ፀጉር በተገዛ ጥፍር
በውሰት ወዘና የተብለጨለጩ
ማኪያቶ ከበው
ለውስኪ ሚንጫጩ
ጅናም ጅንሳም ወንዶች በሴቶች ጫጫታ የሚቁለጨለጩ
.
ይገርማል ጎዳናው ይገርማል መንገዱ....
.
ድንቡሽቡሽ ህፃናት
በቶም ኤንድ ጄሪ ሱስ
ቀልባቸው የከሳ
በአይፎኑ አጮልቆ
ያንጀሊናን ከንፈር የሚስም ጎረምሳ
.
ቀውጢ ዳያስፖራ
.
የሎቲው የቁምጣው የቲሸርቱ ጥለት የተንዘረፈፈው
አማርኛ ሲሸሽ "what's happen" የጠለፈው
.
ነቄ ብላቴና
.
ከዮፍታዬ ቀዬ
ካ'ዲስ አለማየሁ
ከመዝገቡ መንደር
የአዲስ አ'ባ ጥሪ
በቁምጣ ያበረረው
ከቅኔ ተጣልቶ
ከግዕዝ ተኳርፎ ሎተሪ ሚያዞረው
.
ፀዴ ብላቴና
.
ከባላገር ዘመን
ከጨለማ ዘመን
ወደ ብርሃን ጥግ ተሸጋገርኩ ብሎ
በሸንኮራ ምርኩዝ ከተማ ሚያካልል መቋሚያውን ጥሎ
ነብሱ እየሰለለች
በከተሜነት ወግ ባ'ራዳነት ልምሻ
ሲያዘግም የሚውል
ሊስትሮውን ጭኖ በታቦት ትከሻ
.
ፎቆቹ
.
በመስታወት ቁመት በቆርቆሮ ገፆች
ባ'ልሙኒየም ጥራዝ የተብረቀረቁ
የጌቶቻቸውን እድሜ ሚያሳብቁ
ሁሉም........ ሁሉም......ሁሉም ጥግ ናቸው
ለወደቀ ወገን ይራራል ልባቸው
.
ሁሉም
...... ሁሉም
.
ከዘለለት ጥድፊያ
ከሰርክ ውጣ ውረድ በተረፈች አንጀት
ለወደቀ ወገን ምርኩዝ ማበጃጀት
ሁሉም...... ሁሉም ይችላሉ
ስለ'ግዚአር ላለ ይመፀውታሉ
.
እኔ ግን........ እኔ ግን .........ቆጥራለው
የ'ድሜ ክቡር ጀንበር
በጎዳና ፅልመት ሲዋጥ አስተውላለው
ጡረታ መንገድ ዳር ሲከፈን አያለው
.
ቆጥራለው.....ቆጥራለው
.
ቆጥራለው አዛውንት
በየአቀበቱ በየቁልቁለቱ
ማረፊያ ፍለጋ የሚንከራተቱ
ቆጥራለው አዛውንት ከልጆቻቸው ፊት
የልመና መዝገብ የገለጡ አሮጊት
ቆጥራለው በየመንገዱ ዳር
እርጅና ሙሽራው ለምፅዋት ሲዳር
ቆጥራለው በየሸንተረሩ በየተፋሰሱ
አቀርቅሮ ሲያዘግም እርጅና ሞገሱ
ቆጥራለው በ'ያደባባዩ
የሽማግሌ አይኖች የልጅ ፊት እያዩ
ቆጥራለው በየሰርጣሰርጡ
በልመና ጉልበት ከሞት ሲፋጠጡ
የ'ርጅና መዳፎች እሾህ ሲጨብጡ
.
ቆጥሬ..... ቆጥሬ.......ቆጥሬ
በለማኝ አዛውንት ብዛት ተሳክሬ
የማሰንበቻ ስንቅ ከኪሴ ቆንጥሬ
ያፅድቆቴን ዋጋ በሳንቲም መንዝሬ
ባ'ዛውንት ምርቃት ከሀገር ከቀዬው ትርፌን ሳመሳስል
በጎዳናው ቀለም ፃድቅ መልኬን ስስል
ጎልቶ ሚታየኝ ግን የሚያሳፍር ምስል
በቀላል ጥያቄ የነተበ ምስል
.
ጥያቄ
.
የዲጄ ኳኳታ የደናሽ ጋጋታ
የድራፍት እርካታ ያ'ረቄ ድንፋታ
ባጣበበው መንገድ
እንደምን ይቻላል
ላ'ያት ሳንቲም ሰጥቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለወጣት ሹክሹክታ ለገደል ዝምታ
ላስመሳይ ጫጫታ ላድርባይ እሪታ
በተሰራ መንገድ
እውነት ቀላል ነው ወይ
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለቡቲክ ሰልፈኛ ለካፌ 'ድምተኛ
ለውስኪ ጭሰኛ ለበርገር ምርኮኛ
በተሰራ መንገድ
እንደምን ይቻላል
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
አያት....አያት...አያትነት ማለት
በደማቅ አሻራ የሸመኑት ጥለት
ለተራኪ እድሜ የተሰጠ አንደበት
ባ'ባት በ'ናት ፅናት የማይደክም ጉልበት
በልጅ ልጅ መነፅር የማያረጅ ውበት
በልጅ ልጆች ጥበብ የሚታደስ እውቀት
.....................................የሚታደስ እውነት
አያት ሆኑ ማለት
ድርብ አባትነት
ድርብ እናትነት
.
በተለይ እዚህማ.......
በዚህች አይነት ሀገር
ጎጆዋን ላቆመች
በተጋድሎ ካስማ
ባርበኝነት ማገር
በዚህች አይነት ሀገር
ጥያቄና መልሷን
ባ'ዛን በቅዳሴ በምትሰራ መንደር
በዱአ በፀሎት
በምናኔ ምርኩዝ በከረመች ሰፈር
የአያትነት ዋጋው በልኩ ቢሰፈር
ለሳንቲም ምርቃት ባልተሻማን ነበር!
.
ታሪክ በመዳፉ ስላደላደለው
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ንጉስ አያት አለው
የልጅ ልጆች ስባት ባያመነምነው
ያያቶቻችን መልክ ሁሌም አንድ አይነት ነው
.
እላለው... እላለው....
.
የልጆች ምፅዋት ያ'ያቶች ልመና
ያ'ባቶች ግርግር በሞላው ጎዳና
መንገዱ አይልቅም
ጎዳናው አያልቅም
ይሰፋል ይረዝማል ይሄዳል ይጓዛል
እግረኛው ሞኝ ነው
ሳንቲሙን ዘርዝሮ
ከወደቁ አዛውንት ምርቃት ይገዛል
.
መንገዱ ያስፈራል
መንገዱ ይጨንቃል
ልጆች ሳቅ ሲያንቃቸው
አያት እምባ ይጨምቃል
መንገዱ ያሰጋል መንገዱ ያረጃል
ከዘናጭ ልጆች ጎን እርዛት ያዘለ አያት ይወለዳል
.
ሰጪ ካለቀሰ ተበዳሪ ስቆ
ጌታ ከለመነ አማኙ 'ግር ወድቆ
ልዑል ከዘመረ ንጉሱ ተዋርዶ
ገፁ ተመሳቅሎ ሽፋኑ ካማረ
ወለሉ ተንቆ ምንጣፍ ከከበረ
ባ'ገርኛ ስሌት ማነው ያልከሰረ?
.
እላለው........እላለው
.
ከየጎዳናው ገፅ ጥያቄ አነሳለው
ጥያቄ እጥላለው
እርጅና ለማምሻው ጎዳናን ካመነ
አያት ከልጅ ልጁ ሳንቲም ከለመነ
ባገርኛ ስሌት ማነው ያልመከነ?
.
በ'ግዚኦታ ዘመን በምዕላ ዘመን
እመንገድ ዳር ወድቆ ትራፊ መለመን
በጥሞና ዘመን የሚያስቡት ማጣት
በማውረሻ እድሜ የሚሰጡት ማጣት
በማልበሻ ዘመን በ'ርዛት መቀጣት
በለጋሽነት ወቅት በማጉረሻ ዘመን
በጥማት መገረፍ በርሀብ መመንመን
ከሆነ እጣችን
ይጠየቅ ትርጉሙ የልጅነታችን
ይፈተሽ መንገዱ የልጅ ልጆቻችን

ግድ የለም እንመን

እንመን

በሰውኛ ስሌት ውጤቱ ሲሰራ
ትውልድ ያደኸያል ያያቶች ኪሳራ
በልጅ ልጆች ዓለም
እንደጉድ ቢደለቅ ቢዘመር ቢዘፈን
አባት ይወራጫል ባ'ያቶች መታፈን
.
አባት ሆይ
.
ለልጆችህ ርዕዮት
ትላንቱን የረሳ ተስፋ ሲደራረት
ህልሜ ነው ይልሀል ያ'ያቶቹ ቅዠት
ከልጅህ አንደበት
ቋንቋ እንደዶፍ ቢዘንብ
ትርጉም ቢንፎለፎል ሺ ቃላት ቢጎርፍም
የልጅ ልጅ አግባቢ ግማሽ ገፅ አይፅፍም
ከልጆችህ ባህር
አሳ የሚያጠግቡ ለአሳ ሚስማሙ
እፅዋት ተክሎች
እንደጉድ ቢራቡ እንደጉድ ቢያብቡ
ገበታው አይሞላም ተቀዷል መረቡ
.
ግድ የለም እንመን........እንመን
.
የስኬት ክብደቱ
የምቾት አይነቱ
የነገ ውበቱ ባሻው ቋት ቢለካ
በምንም ቢሰፈር ባሻው ቃል ቢነገር
ጀግና ልጅ አትወልድም
አያቶቿን ገድላ የምትሸልል ሀገር
.
ከፎቆቹ ጥላ....
ከያስፓልቱ ገላ ሲታተም ድምቀቴ
በመስታወት አጀብ ሲጠገን ጉልበቴ
ይኸው አነበብኩት
አያቶቼ ፊት ላይ ተፅፏል ሽንፈቴ
በመኪና ብዛት
በመስታወት አይነት ሲለካ ፍጥነቴ
በግንብ አጥር መአት
በፎቆች ጋጋታ ሲሰላ ስኬቴ
ይኸው ይታየኛል
አያቴ ገፅ ላይ ተስሏል ውድቀቴ

ተስሏል ሽንፈቴ!

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።


Thursday, March 3, 2022

ፕሮፌሰር ሐይሌ ገሪማን በጨረፍታ

 A Glimpse of Prof Haile Gerima
 *************************** 
(የዘመን አቆጣጠሩ ሁሉ እንደ አውሮፓውያን ነው ) ከአሥር ልጆች አራተኛ በመሆን የተወለደው ኃይሌ ገሪማ መጋቢት 1946 ላይ ነው ይችን አለም የተቀላቀለው ፡፡ እናቱ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ ሲሆኑ አባቱ አቶ ገሪማ ታፈረ ደግሞ የተውኔት እና የቴአትር አዘጋጅ ነበሩ፡ እንደ ሳንኮፋ ድረገጽ ከሆነ ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ ገና በወጣትነት ዘመኑ የአባቱን ፈለግ በመከተል በአባቱ ቲያትሮች ይለማመድ ነበር ፡፡ ሃይሌ እና እህቱ ዘመናዊ ትምህርት ቤት በመሄድ በቤተሰባቸው ውስጥ የመጀመሪያዎቹ እንደሆኑ ድረገጹ ጠቅሶ የሃገሩን ባህል እና ሥርዓተ ትምህርት በማስተማር እና ለአሜሪካ የሰላም ጓድ አባላት እንዴት ፊደል መጻፍ እንደሚቻል በማስተማር እንዲሁም ባህሉን በማስተዋወቅ የድርሻውን ተወጥቷል ፡፡ 
ፕሮፌሰር ሃይሌ. "ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በፈጠራ ጥበብ ማዕከል ውስጥ አጭር ቆይታ ካደረገ በኋላ, ድራማ ለማጥናት ወደ አሜሪካ አቅንቷል፡፡ እዚያም ሸሪኪያና ከተባለች ሴት ጋር በትዳር ተጣምሮ አምስት ልጆችን አፍርቷል፡፡ በሎስ አንጀለሰ ከተማ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ከ1976 ጀምሮ የፊልም ጥበብን በማስተማር ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል ፡፡ 
የፊልም ጥበብ ቀማሪው ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ ከሰራቸው ፊልሞች መካከል 
አወር ግላሰ ፣ 
ቻይልድ ኦፍ ሬንሰንስ ፣ 
ቡሽ ማማ የተባሉ ስራዎችን በ1975 የሰራ ሲሆን 
ስሪ ታውዘንድ የተሰኘ ፊልም በ1976 ፣ 
ዊልምግተን ፣ ቴን ዩ ኤስ ኤ ቴን ታውዘንድ የተሰኘን ፊልም በ1977 
አሽስ ኤንድ ኢምበርስ በ1982፣ 
አፍተር ዊንተር ስተርሊን ብሮውን በ1985 ፣ 
ሳንኮፋ በ1993 
አድዋ አን አፍሪካን ቪክትሪ በ2000 የሰራ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ተሸላሚም ነው፡፡ የፓን አፍሪካን የፊልም አዘጋጆች ፌዴሬሽን እና የአፍሪካን የፊልም አዘጋጆች ኮሚቴ አባልም ነው ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ፡፡ 

ከሰራቸው ፊልሞች መካከል:- 
 • 1972 - Hour Glass Hour Glass 
• 1972 - Child of Resistance 
• 1976 - Bush Mama 
• 1976 - Mirt Sost Shi Amit (also known as Harvest: 3,000 Years) 
• 1978 - Wilmington 10 -- U.S.A. 10,000 
• 1982 - Ashes and Embers 
• 1985 - After Winter: Sterling Brown 
• 1993 - Sankofa 
• 1994 - Imperfect Journey 
• 1999 - Adwa - An African Victory 
• 2009 - Teza Over the course of his career, Gerima has received numerous awards and distinctions in film festivals:- 
• 1976 - Grand prize / Silver Leopard for Harvest: 3,000 Years- Locarno 
• 1982 - Grand Prix Award for Ashes and Embers-Lisbon International Film Festival 
• 1983 - FIPRESCI Film Critics Award for Ashes and Embers-Berlin International Film Festival 
• Outstanding Production Ashes and Embers - London Film Festival 
• 1984 - Tribute Festival De la Rochelle, France 
• 1987 - Long Metrage De Fiction-Prix de la Ville de Alger for Ashes and Embers 
• 1993 - Best Cinematography Award for Sankofa, FESPACO, Burkina Faso 
• 2003 - Lifetime Achievement Award, 4th Annual Independence Film Festival, Washington D.C. 
• 2006 - Festival De Cannes Selection Official Cannes Classic -Harvest: 3,000 Years 
• 2008 - Venice Film Festival Special Jury Prize and Best Screen Play Award - Teza 
• 2009 - Jury Award at the 18th International Film Festival Innsbruck/Austria - Teza 
• 2009 - Golden Stallion of Yennenga at the FESPACO African Film Festival - Teza http://www.rfi.fr/ actuen/articles/111/article_3102.asp 
• 2009 - Dioraphte Award Hubert Bals film in highest audience regard at the Rotterdam Film Festival 
• 2009 - Golden Tanit/Best Film Award for its "modesty and genius," Best Music (Jorga Mesfin Vijay Ayers), Best Cinematography (Mario Massini), Best Screenplay (Haile Gerima), Best Supporting Actor Abeye Tedla at the Carthage/Tunisia Film Festival for Teza 
• 2009 - Golden Unicorn and Best Feature Film at the Amiens/France International Film Festival France for Teza 
• 2009 -The Human Value's Award at the Thessaloniki Film Festival in Greece for Teza 
• 2009 - Official Selection at the Toronto Film Festival for Teza 
 ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ በሚሰራቸው የፊልም ጥበቦች ሃገሩን በማሰተዋወቅ ባለውለታ እንደሆነ ብዙዎች ይመሰክሩለታል፡፡ ወደፊት በሚያበረክታቸው የፊልም ስራዎቹ ውስጥ ለሃገሩ ልዩ ቦታ እንደሚሰጥ ተናግሯል፡፡
ከጎንደር ተራሮች እስከ ሺካጎ አሜሪካ ------- 
እ.አ.አ በ1976 በምርጥ Feature Film ዘርፍ የሚቼክስ አዋርድን ወስደዋል፣ በፓን አፍሪካን የፊልም እና የቴሌቪዥን ፌስቲቫል ላይ ደግሞ ምርጥ ሲኒማቶገራፈርም እርሳቸው ነበሩ፣ እ.አ.አ በ1993 በከንቲባው አርቲስት አዋርድ የላቀ አርቲስቲክ ዲሲፒለን ተሸላሚው በዋሽንግተን ዲሲ አሁንም የእኛው ሰው ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካን የፊልም ባለሙያዎች አባልና ኮሚቴም ናቸው፡፡ 
 እ.አ.አ በ1975 Hour Glass, Child of Resistance, Bushmama፣ እ.አ.አ በ1976 Harvest: 3000 Years፣ እ.አ.አ በ1977 Wilmington 10-USA 10,000፣ እ.አ.አ በ1982 Ashes and Embers፣ እ.አ.አ በ1985 After Winter, Sterling Brown፣ እ.አ.አ በ1993 Sankofa፣ እ.አ.አ በ2000 Adwa: An African Victory፣ ጤዛ.. የመሳሰሉትን ፊልሞች ለእይታ አብቅተዋል፡፡ 
 እ.አ.አ ከ1976 ጀምሮ በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ፐሮፌሰር ሲሆኑ ማይፊደህ ፊልም የተሰኘው የፊልም አከፋፋይ ድርጅት እና ሳንኮፋ ቪዲዮና መጽሐፍ መደብር እንዲሁም ኔጎድጋድ ፊልም ፕሮዳክሽንም ባለቤት ናቸው፡፡ ታሪክ ዘመኑን እ.አ.አ መጋቢት 4 1946 ነበር ብሎ መዝግቦታል፡፡ ቦታውም ጎንደር፡፡ 
ለፀሀፊውና ድራም ተጫዋቹ አባቱ እና ለመምህሯ እናቱ 4ኛ ልጅ ሆኖ ሲወለድ ወደፊት አፍቃሬ አፍሪካ እና ስመ ጥር የፊል ባለሙያ ብሎም ፐሮፌሰር ይሆናል ብሎ የጠረጠረ ስለመኖሩ እንጃ፡፡ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ! በገጠራማ አካባቢዎች በመዞር የድራም ብቃታቸውን ያሳዩ የነበሩት አባቱ በህይወቱ የመጀመሪያው ተፅዕኖ አሳራፊ እንደነበሩ ይናገራል፡፡ ታዲያ ልጅ ሳለ የቅኝ ግዛት ስርዓት በፊልም ላይ ያለው እምብዛም በንቃት ስለማይታወቀው ተፅእኖው ይወያይ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ታዲያ በፊልም ላይ የተመለከቷቸውን ነገሮች በማስመሰል ለመጫወት ይሞክሩ ነበር፡፡ በገጠራማ አካባቢዎች በመዞር የድራም ብቃታቸውን ያሳዩ የነበሩት አባቱ በህይወቱ የመጀመሪያው ተፅዕኖ አሳራፊ እንደነበሩ ይናገራል፡፡ ታዲያ ልጅ ሳለ የቅኝ ግዛት ስርዓት በፊልም ላይ ያለው እምብዛም በንቃት ስለማይታወቀው ተፅእኖው ይወያይ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ታዲያ በፊልም ላይ የተመለከቷቸውን ነገሮች በማስመሰል ለመጫወት ይሞክሩ ነበር፡፡ 
ወደ ጎንደር ተራሮች በመሄድ የካውቦይ እና የህንዶችን ገፀ ባህርይ ይጫወታሉ፡፡ ካውቦዮች እንዴት አድርገው ህንዶችን ድል እንዳደረጓቸው የሚያሳዩ ገፀባህርይዎችን መልሰው መላልሰው ሲጫወቱ ይውላሉ፡፡ በሚገርም ሁኔታ ግን እነዚህን ገፀ ባህርይዎች ሲጫወቱ የህንዶች ደጋፊ ናቸው መባል አይፈልጉም አልያም ካውቦዮች እንዲያሸንፉ አንዳች ፍላጎት አልነበራቸውም፡፡ ይህን ጉዳይ ፕፌሰሩ ሲያስረዱ “ሌላው ቀርቶ በታርዛን ፊልም ላይ እንኳን እንቅስቃሴዎችን እምንመለከታቸው ከአክተሩ የእይታ ቦታ ሆነን ታሪኩ ከየትኛው የእይታ ነጥብ ተነስቶ የት ይደርሳል የሚለውን ነበር እምንከታተለው፣ በቃ ሙሉለሙሉ ትኩረታችንን የሚይዘው የታሪኩ አወቃቀር ነበር፡፡ ልክ አፍሪካዊዎች አድብተው ሊይዙት ሲሞክሩ ታርዛን ማን እንደመጣበት አይቶ እንዲጠነቀቅ እንጮህለት ነበር፡፡” ይላሉ፡፡ ምናልባት የፊልም ሙያ የፕሮፌሰሩን ቀልብ የገዛቸው በዚህ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም፡፡ 
 ወደ አሜሪካ መሄድ -------- እ.አ.አ በ1966 ወደ አሜሪካ በመሄድ ሺካጎ Goodman School of Drama ውስጥ በመግባት የትወና ትምህርት ይከታተል ገባ፡፡ ስለዚህ ጉዳይ በሎስ አንጀለስ ታይምስ ጋዜጣ ላይ የሚከተለውን አስፍሯል “እያደግሁኝ ስመጣ በቴኣትር መሰራት ፈልጌ ነበር ነገር ግን የሆሊውድን ፊልሞች እየተመለከትሉ ማደጌ ወደፊልሙ እንዳዘነብል አድርጎኛል፡፡ በርግጥ በጊዜው ፊልም መስራት በአገሪቱ መንግስት የሚበረታታና የሚደገፍ ነገር አልነበረም፡፡” ኋላ እ.አ.አ በ1970 ወደ ካሊፎርንያ ተጓዘ፡፡ በዚያም ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ በመግባት በFine Arts ዘርፍ የባችለርና ኋላም የማስተርስ ዲግሪውን በእጁ ማስገባት ቻለ፡፡ 
/አንድ ለመንገድ/ -------- በነገራችን ላይ ህይወት በአሜሪካ ለፕሮፌሰሩ ያን ያክልም አልጋ በአልጋ አልነበረችም፡፡ በተለይ የልጅነት ህልማቸውን ለማሳካት የተጓዙበት ርቀት የዓላማ ፅናታቸውን በሚገባ የሚያመላክት ነው፡፡ ለምሳሌ፣ ሆሊውድ ፊት ነሳው፣ ፊልሙን ለመቅረፅ ፈንድ የሚያደርገውም እስከማጣት ደረሰ፡፡ በዚያም በዚህም ብሎ ፊልሙን ቀረፆ ሲጨርስ ደግሞ የሚያከፋፍልለት ጠፋ፤ ይሄኔ እጅ መስጠት በዚያ የለችምና የሚልም አከፋፋይ ድርጅት አቋቋመ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቪዲዮ አከራዮች ያንተን ፊልም በመደብራችን ማስቀመጥ አንፈልግም ሲሉት የቪዲዮ መደብር ከፈተ፡፡ ሁሉን በታላቅ ፅናትና ትግል አልፎ ፊልሞቹን ቴኣትር ቤት ለማገባት ሄደ፣ በራቸውን ዘጉበት፡፡ እና ምን ተሻለ? ለምን በየአገራቱ የሚገኙ ቴኣትር ቤቶችን ተከራይቼ ፊልሜን አላሳይም አለ፡፡ አደረገው፡፡ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ! የእኛ ሰው! *********************************************************************
Source:-- Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) facebook page 
https://sewasew.com


ፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ ከሸገር ሬድዮ ለዛ ፕሮግራም አዘጋጅ ብርሃኑ ድጋፌ ጋር ታህሳስ 18 ቀን 2001 ዓ. ም.
Professor Haile Gerima With Berhanu Digaffe on ShegerFm Leza Program


"አያቱ ኢንተርስት ያላደረገችው ፊልም ሰሪ ለኔ ፊልም ሰሪ አይደለም" ፕሮፌሰር ሐይሌ ገሪማ ..ጥበብና_ ትውልድ_ ክፍል ፩



'የኢትዮጵያ ትያትር የመቶ ዓመት እድሜ ነው ' የሚባለው ስኽተት ነው "ትያትር ራሱ የተጀመረው አፍሪካ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው"_ፕሮፌስር ሐይሌ ገሪማ_ክፍል ፪



"አንድ ከነገሠ ሰው ጋር ጊዜውን የሚያጠፋ አርቲስት አርቲስት ሳይሆን ፖለቲሻን ነው" ጥበብ-እና- ትውልድ _ክፍል ፫


ሰይፍ ፋንታሁን በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ከፕሮፌስር ሐይሌ ገሪማ_

Seifu Fantahun show interview with Haile Gerima_2014

ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ ይባላሉ በዋሽንግተን ዲሲ ሀዋርድ ዩኒቨርስቲ የፊልም ጥበብ ፕሮፌሰር ናቸው።
***********************************************************

☀️በውጪው አለም በተለይም በጥቁር አሜሪካውያን ዘንድ የሚታወቁት ብዙ ሽልማትንም የተቀበሉት ሳንኮፋ (Sancofa) በሚባል ፊልማቸው ነው።

☀️ Sankofa በጋናውያን 'Akan Twi' እና 'Fante' ቋንቋ የራስ የሆነን ነገር ግን ጠፍቶ የነበረን ነገር መልሶ ማግኘት የሚል አንድምታ አለው።
ይህንን ሀሳብም ለመግለፅ ወደፊት የምትሄድ ነገር ግን ፊቷን ወደኋላ ያዞረች በአፏ እንቁላል የያዘች ወፍ ምስል ይጠቀማሉ።

☀️በተጨማሪም ፕሮፌሰር ሐይሌ ገሪማ ይህንን ፊልም በሚሰሩበት ጊዜ የጋናዊዋ ባለቤታቸው አስተዋፆ እንዳለበት ተናግረዋል።

☀️እሳቸውም ጥቁር አሜሪካውያን ሆይ የመጣችሁበትን ዘወር ብላችሁ ተመልከቱ የጠፋባችሁን ፈልጉ ሲሉ በፊልሙ አመልክተዋል።
☀️አገር ወዳድነታቸው ዳር የለውም ከአማርኛ ፊልሞቻቸው ጤዛ የሚለው ያንን ትውልድ ከዚህኛው ያስተያየንበት የትላንቱን ኩነት የገመገምንበት የፊልም ጥበብን የተረዳንበት ነው።

☀️ፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ ከ'ጤዛ' በተጨማሪ
* የ 3000 ዘመን ምርት
* Sankofa
* Adwa
* Bush Mama
* Imperfect Journey (Documentary
* Ashes and Embers
* Child of Resistance
እና ሌሎችም የፊልምና የዶክመንተሪ ስራዎች አሏቸው።

😉እነዚህን ስራዎች ሲሰሩ የትኛውንም የነጭ የገንዘብ እርዳታ ላለመጠየቅ በሚል የተቋቋመ Sankofa የሚባል የመፅሐፍ መሸጫ መደብር አቋቁመዋል። እዛችው ክፍል ውስጥ ከመፅሐፍ መሸጥ በተጨማሪ በጥቁሮች እና በአፍሪካውያን ታሪክ፣ ባህል፣ ስልጣኔ፣ ነፃነት እና የአኗኗር ዘይቤ ላይ የሚያተኩሩ ጥናታዊ ፅሑፎች አና ውይይቶች በተለያዩ ጊዜዎች ያካሔዳሉ።

EBS tv Riyot Tewodros Tsegaye interview with professor Haile Gerima part_1



EBS tv Riyot Tewodros Tsegaye interview with professor Haile Gerima part_2


EBS tv Riyot Tewodros Tsegaye interview with professor Haile Gerima part_3


EBS tv Riyot Tewodros Tsegaye interview with professor Haile Gerima part_4




EthioTube Presents Legendary Ethiopian Filmmaker Haile Gerima __June 2015

https://www.youtube.com/watch?v=Mh591qME_bM

 

https://www.youtube.com/watch?v=UoqoecV4jLo 

 


Wednesday, August 4, 2021

ኢትዮጵያና ኦሎምፒክ

 ኦሎምፒክና የኢትዮጵያ ወርቃማ ኦሎምፒያኖች_ግሩም ሠይፉ( አዲስ )

 


1896 እኤአ ላይ የግሪኳ አቴንስ ከተማ ካስተናገደችው የመጀመርያው ኦሎምፒድ አንስቶ ባለፉት 125 ዓመታት ውስጥ በተካሄዱት 31 ኦሎምፒያዶች ኢትዮጵያ 13 ተሳትፋለች፡፡ በኦሎምፒክ መድረክ ሁሉንም ሜዳልያዎችን የሰበሰበችው በአትሌቲክስ ስፖርት ብቻ ሲሆን በከፍተኛ የውጤት ታሪካቸው ከሚጠቀሱ 8 አገራት አንዷ ናት። አፍሪካን በመወከል ደግሞ ከኬንያ ቀጥሎ ከፍተኛውን ስኬት አስመዝግባለች፡፡
የጃፓኗ ቶኪዮ ከምታስተናግደው 2020 32ኛው ኦሎምፒያድ በፊት ኢትዮጵያ በተካፈለችባቸው 12 ኦሎምፒያዶች 227 ኦሎምፒያኖች (168 ወንድ እና 59 ሴትተሳትፈዋል፡፡ ከእነሱም መካከል 32 ኦሎምፒያኖች 1 እስከ 3 ባሉ ደረጃዎች ስኬታማ በመሆን 54 ሜዳልያዎችን (22 የወርቅ፤ 11 የብርና 21 የነሐስ) ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል፡፡
ከሜዳልያዎቹ ስብስብ 22 የወርቅ ሜዳልያዎችን ለኢትዮጵያ ያጎናፀፉት 13 ኦሎምፒያኖች ናቸው፡፡ በተረፈ 11 የብር ሜዳልያዎች 10  እንዲሁም 21 የነሐስ ሜዳልያዎች 18 የኢትዮጵያ ኦሎምፒያኖች ተገኝተዋል፡፡

የወርቅ ሜዳልያ ክብርና ዋጋ
ኦሎምፒክ የዓለም አገራትና ህዝቦቻቸውን በአንድ መንፈስ የሚያስተባብር መድረክ ነው፡፡ በስፖርት መድረኩ በድህነት የተጎሳቆሉ፤ በበቂ የስፖርት መሰረተ ልማት ዝግጅታቸውን ያላከናወኑ፤ በየአገራቸው ባሉ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች የተረበሹ፤ በጦርነት እና በኢኮኖሚ ቀውስ የሚገኙ አገሮቻቸውን የወከሉ ኦሎምፒያኖች ሲሳተፉ ሁሉም አንድ ዓላማ ይኖራቸዋል፡፡ ይህ ዓላማ በሜዳልያ ክብር አገራቸውን ማኩራትና ሰንደቅ አለማቸውን ማውለብለብ ነው፡፡ የኦሎምፒክ የሜዳልያ ክብር መጎናፀፍ  ደግሞ የየትኛውም የዓለም ስፖርተኛ ህልም እንደሆነ ይታወቃል።
በኦሎምፒክ ታሪክ ሙሉ ለሙሉ ከወርቅ የተሰሩ ሜዳልያዎች ለአሸናፊዎች ለመጨረሻ ግዜ የተሰጠው 1912 እኤአ ላይ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ የኦሎምፒክ ሜዳልያዎች ገፅታ በአዘጋጅ አገራት የዲዛይን ፍላጎት እንዲሆን ቢፈቀድም ሜዳልያዎኙ የሚሰሩበት ማእድን በኦሎምፒክ ቻርተር መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል፡፡ በኦሎምፒክ 1 እና ሁለተኛ ደረጃ የሚሸለሙት የወርቅና የብር ሜዳልያዎች 92.5 በመቶ የሚሰሩት ከብር  እንዲሁም 6 በመቶ ከመዳብ ነው፡፡
3 ደረጃ ተሸላሚዎች የሚሰጡት የነሐስ ሜዳልያዎ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ከነሐስ የተሰሩ ናቸው፡፡ የወርቅ ሜዳሊያዎች 6 ግራም ወርቅ መለበጣቸው ግድ ነው፡፡ ሁሉም ሜዳልያዎች ውፍረታቸው 3ሚሜ  ዲያሜትራቸው 60 ሚሜ መሆን አለበት፡፡ አንድ የወርቅ ሜዳልያን አቅልጦ ይሸጥ ቢባል 706 ዶላር ጀምሮ ዋጋ ይኖረዋል፡፡
30ኛው ኦሎምፒያድ 4700 ሜዳልያዎች ለተሸላሚዎች የተዘጋጁ ሲሆን በሜዳልያዎቹ ስራ 802 ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡  ለኦሎምፒክ ሻምፒዮኖች የቀረቡ 302 የወርቅ ሜዳልያዎች 400 ግራም ይመዝናሉ፡፡


አበበ ቢቂላ
ትውልዱ ደብረብርሃን አቅራቢያ ጃቶ በተባለች ቦታ ነበር፡፡ 1960 እኤአ 83 አገራት የተውጣጡ 5 በላይ አትሌቶች በተካፈሉበት የሮም ኦሎምፒክ ላይ ለአፍሪካ እና ለኢትዮጰያ በኦሎምፒክ ታሪክ የመጀመርያውን ሜዳሊያ በማስገኘት ፈርቀዳጅ ታሪክ ሰርቷል፡፡  በባዶ እግሩ  ሮጦ ታላቁን የኦሎምፒክ ማራቶን በአንደኝነት ከማሸነፉም በተጨማሪ፤ 2162 በሆነ ሰአት አዲስ የአለም ሪከርድ አስመዝግቦም ነበር፡፡  
4 ዓመታት በኋላ 1964 እኤአ የኦሎምፒክ አዘጋጅ የጃፓኗ ከተማ ቶኪዮ ነበረች፡፡ የቶኪዮ ኦሎምፒክ 6 ሳምንታት ሲቀሩት፤ አበበ ቢቂላ የቀዶ ህክምና ተደርገለት። በፍጥነት እንደሚያገግም ተስፋ በማድረግ፤ የኦሎምፒክ ቡድን ውስጥ መካተቱ አልቀረም፡፡
ከቀዶ ጥገናው ሙሉ ለሙሉ ሳያገግም ማራቶኑን በመሮጥ በድጋሚ የኦሎምፒክ ሻምፒዮን ሆኖ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበ፡፡ ድሉ ለኢትዮጵያ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ብቻ አልነበረም  በድጋሚ የዓለም  ማራቶንን ሪከርድ አሻሽሏል - 21211 በሆነ ሰአት በመግባት፡፡ በሁለት ኦሎምፒኮች  በማራቶን አከታትሎ  በማሸነፍ፤ በሁለቱም ሪከርድ በማስመዝገብ እና ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎች በማግኘት፤ አበበ ብቸኛው ኦሎምፒያን ነው፡፡

ማሞ ወልዴ
ማሞ ወልዴ የተወለደው ከአዲስ አበባ 60 .. ርቀት ድሪጂሌ በተባለች የገጠር ከተማ ተወልዷል፡፡ ከአበበ ቢቂላ በኋላ የኢትዮጵያ ብቸኛ ተስፋ አንተ ብቻ ነህ ተብሎ 1968 እኤአ ላይ የሜክሲኮን ኦሎምፒክ የተሳተፈ ነበር፡፡
በሜክሲኮ ኦሎምፒክ 10 ሜትር ውድድር ኢትዮጲያን ወክሎ እንዲሮጥ የተመረጠው አትሌት ማሞ፤ ከከባድ ተቀናቃኞች ጋር ተፎካክሮ በአጨራረስ ብልሃት ስላልነበረው  ውድድሩን በሁለተኛነት ጨርሶ፤ በኦሎምፒክ ተሳትፎው ለራሱ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ተጎናፅፏል፡፡
 ማሞ ወልዴ 10 ሜትር የብር ሜዳልያው ድል በኋላ ግን ከዚህ አድካሚ ውድድር እፎይ የሚልበት ጊዜ አልነበረውም፤ በማራቶን እንዲወዳደርና የአበበን የድል ታሪክ መድገም እንደሚኖርበት የኢትዮጲያን ክብር የማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት በወቅቱ አሰልጣኝ የነበሩት አሰልጣኝ ንጉሴ ሮባ ተነገረው፡፡ 10 ሜትር ተወዳድሮ የብር ሜዳልያ ባገኘ በማግስቱ ነበር ማራቶኑ፡፡ ለመፎካከር ከተሰለፉት 44 አገራት አትሌቶች ውስጥ፤ ከኢትዮጲያ አበበ ቢቂላ፤ ማሞ ወልዴና ደሞሴ ነበሩበት፡፡ 15 ኪሎ ሜትር  ያህል  ሲመራ የቆየው የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ በህመም ውድድሩን አቋርጦ ለመውጣት ተገደደ፡፡ የስፖርት አፍቃሪዎች ልብ በሃዘን ተሰበረ፡፡  ጀግና ጀግናን እንደሚተካ የተዘነጋ ይመስላል፡፡  
በአበበ ቢቂላ በተከታታይ ሁለት ኦሎምፒክ ድል የተገኘበትን የማራቶን ውድድር ማሞ ወልዴ በድጋሚ አሸንፎ ታሪክ በመስራት የኢትዮጵያን ክብር አስጠበቀ፡፡ 35 አመቱ በአንድ ኦሎምፒክ ሁለት ሜዳሊያ ያጠለቀው ማሞ፤ ጀግንነቱ ለኢትዮጵያውን ኩራትንና ደስታን አጎናፀፈ፡፡ ከዚህ ስኬቱ በኃላ አትሌት ማሞ ወልዴ 1965 በጀርመን ሙኒክ በተካሄደው ኦሎምፒክ 10 ሜትር ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡


ምሩፅ ይፍጠር
ምሩፅ ይፍጠር በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ውስጥ በአዲግራት ተወለደ፡፡ በወጣትነቱ ከጋሪ ነጂ ጀምሮ፤ በተለያዩ ፋብሪካዎች ተቀጥሮ ሰርቷል፡፡
ለመጀመርያ ጊዜ በኦሎምፒክ የተሳተፈው የጀርመኗ ከተማ ሙኒክ ባስተናገደችው ኦሎምፒክ ሲሆን በአስር ሜትር ሶስተኛ ወጥቶ የነሃስ ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡በ1980 እኤአ የራሽያ ዋና ከተማ ያስተናገደችው የሞስኮ ኦሎምፒክ የምሩፅ ነበር፤ አለምን ጉድ ያሰኘበት፡፡ በሞስኮ ኦሎምፒክ 10ሺና 5 ሜትር ኢትዮጵያን በመወከል የተወዳደረው ምሩፅ፤  በፍፁም ብቃት በሁለቱም በማሸነፍ ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎችን ያገኘ ሲሆን በሁለቱም ርቀቶች በኦሎምፒክ ያሸነፈ የመጀመርያው አትሌት ነበር፡፡



ደራርቱ ቱሉ
ደራርቱ ቱሉ ትውልዷ በአርሲዋ ትንሽ ከተማ በቆጂ ነው፡፡  አትሌት ደራርቱ ቱሉ ለኢትዮጲያዊያን ብቻ ሳይሆነ ለአፍሪካዊያን እንስት አትሌቶች ፈርቀዳጅ የሆኑ ድሎችን በአለም አቀፍ ደረጃ ታሪክ ሠርታለች፡፡
በተለይ ደግሞ የሚጠቀሰው  1992 .. በስፔን ባርሴሎና በተከናወነው ኦሎምፒክ  10 ሜትር የወርቅ ሜዳልያ መጎናፀፏ ነው፡፡ ይህ ድል በአፍሪካ የኦሎምፒክ ታሪክ በረጅም ርቀት በሴቶች የመጀመርያው ድል ነበር። 2000 እኤአ በአውስትራያ በተካሄደው የሲድኒ ኦሎምፒክም ደራርቱ 10 ሜትር ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለመጎናፀፍ በቅታለች፡፡ በተጨማሪም 2004 እኤአ በአቴንስ ኦሎምፒክ 10 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡

 




ፋጡማ ሮባ
አትሌት ፋጡማ ሮባ  የተወለደችው በአርሲዋ በቆጂ ከተማ ነው፡፡ 1996 .. ላይ የአሜሪካዋ አትላንታ ባስተናገደችው ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን በታሪክ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ለኢትዮ ለመጎናፀፍ በቅታለች፡፡

 


 ኃይሌ ገብረስላሴ
ትውልዱ በአርሲዋ ትንሽ ከተማ በቆጂ ነው። ኃይሌ /ሥላሴ ለመጀመርያ ጊዜ 1996 .. ላይ በአትላንታ ኦሎምፒክ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ በመሳተፍ 10 ሜትር ውድድር ተካፍሎ በአስደናቂ የአጨራረስ ብቃት በማሸነፍ የመጀመሪያውን የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል፡፡
2000 .. ላይ 20ኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ ኦሎምፒክ በአውስትራሊያ ሲድኒ ከተማ ሲካሄድ ኃይሌ 10 ሜትር በተካሄደው ውድድር  ከቅርብ ተቀናቃኙ የኬንያው አትሌት ፖልቴርጋት ጋር ያደረገው እልህ አጨራረስ ትንቅንቅ 0.09 ሰኮንድ ልዩነት በመቅደም 2ኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለመጎናፀፍ በቅቷል፡፡

 


ሚሊዩን ወልዴ
አትሌት ሚሊዩን ወልዴ ትውልዱ በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ 2000 .. በአውሰትራሊያ ሲዲኒ በተከናውነው 27ኛው ኦሎምፒያድ አዲስ እና ፈርቀዳጅ ታሪክ ለኢትዮጰያ አትሌቲክስ በማስመዝገብ ተሳክቶለታል፡፡  
በወቅቱ 22 ዓመት ወጣት የነበረው አትሌት ሚልዩን በተካፈለበት 5 ሜትር ውድድር አሸንፎ በርቀቱ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ሲያስመዘግብ በመጨረሻዎቹ 200 ሜትሮች ድንቅ የአጨራረስ ብቃት በማሳየት  ነበር፡፡


ገዛሐኝ አበራ

የአትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው አርሲ የተወለደው ገዛሐኝ በኢትዮጲያ የኦሎምፒክ ተሳትፎ ታሪክ ማሞ ወልዴ ካስመዘገበው የወርቅ ሜዳልያ በኋላ በማራቶን ሊያሽንፍ የበቃ አትሌት ነው፡፡
2000 እኤአ በሲዲኒ ኦሎምፒክ ላይ ገዛሐኝ በማራቶን የወርቅ ሜዳልያውን ሊጎናፀፍ የበቃ ሲሆን  22 ዓመቱ በኦሎምፒክ ታሪክ የመጀመሪያው ወጣት የማራቶን ባለድል ለመሆን ፈርቀዳጅ ታሪክ ለመስራት የቻለበት ነበር፡፡



ቀነኒሳ በቀለ
ትውልዱ በአርሲ በቆጂ የሆነው ቀነኒሳ 10 ሜትር ሶስት ጊዜ 5 ሜትር አንድ ጊዜ በአጠቃላይ 4 የኦሎምፒክ የወርቅ እንዲሁም በሺ ሜትር 1 የብር ሜዳልያዎችን በተጨማሪ በማስመዝገብ በወንድ አትሌቶች በኦሎምፒክ መድረክ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበ ነው፡፡
ቀነኒሳ በኦሎምፒክ መድረክ የመጀመርያ ተሳትፎው 28ኛው ኦሎምፒያድ በግሪክ አቴንስ ላይ የነበረ ሲሆን፤  አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዘገብ ለራሱ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ለማጥለቅ በቃ፡፡ በወንዶች 5 ሜትር ደግሞ የብር ሜዳልያ ነበረው፡፡
4 ዓመታት በኋላ የቻይናዋ ዋና ከተማ ባስተናገደችው 29ኛው ኦሎፒያድ በድጋሚ አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዝገብ 10 ሜትር የሻምፒዮናነት ክብሩን አስጠብቆ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ሊያገኝ የበቃ ሲሆን 5 ሜትርም ድል በማድረግ ሌላ የወርቅ ሜዳልያውንም ተጎናፅፏል፡፡ 1980 እኤአ ላይ በሞስኮ ኦሎምፒክ አትሌት ምሩፅ ይፍጠር  5ሺና 10 ድርብ ድል በማግኘት ያስመዘገበውን ታሪክ በመድገምም አስደናቂ ታሪክ ሊሰራ በቅቷል፡፡ 2012 እኤአ ለየእንግሊዟ ከተማ ለንደን ባስተናገደችው 30ኛው ኦሎምፒያድ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 10 ሜትር ለሶስትኛ ጊዜ የወርቅ ሜዳልያ በመጎናፀፍ በታሪክ የመጀመርያው አትሌት ሆኖ አዲስ ታሪክም ሊያስመዘግብ በቅቷል፡፡


ጥሩነሸ ዲባባ
ትውልዷ አርሲ ውስጥ በቆጂ አጠገብ በምትገኝ ጨፌ በተባለች ስፍራ ነው፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ በኢትዮጲያ የኦሎምፒክ ተሳትፎ ታሪክ በሁለቱም ፆታዎች  እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛው የውጤት ክብረወሰን በማስመዝገብ በግንባርቀደምነት ትጠቀሳለች፡፡
ጥሩነሽ ዲባባ በተሳተፈችባቸውየኦሎምፒክ መድረኮች  2004 እኤአ በአቴንስ፤ 2008 እኤአ በቤጂንግ እንዲሁም 2012 እኤአ በለንደን 5 (3 የወርቅና ሁለት የነሐስ) ሜዳልያዎችን በማግኘት ከረጅም ርቀት አትሌቶች በአንደኛ ደረጃ የከፍተኛ ውጤት ክብረወሰን ይዛለች፡፡
እነዚህ ሜዳልያዎች ላይ 5 ሜትር ነሐስ 2004 አቴንስ ላይ፤  10 እና 5 ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎች 2008 ቤጂንግ ላይ፤ እንዲሁም  10 ወርቅ እና 5 ነሐስ ሜዳልያዎች 2012 ለንደን ላይ ያገኘቻቸው ናቸው።
በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ 5 የወርቅ እና ሜዳልያዎች በመሰብሰብ በረጅም ርቀት ብቸኛውን የውጤት ክብረወሰን እንደያዘች ነው፡፡

 


መሰረት ደፋር
አትሌት መሰረት ደፋር ትውልዷ በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ በኦሎምፒክ የተሳትፎ ታሪክ 5 ሜትር ሴቶች ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎችን ያስመዘገበች ምርጥ አትሌት ናት፡፡
የመጀመርያ የወርቅ ሜዳልያዋን ያስመዘገበችው 2004 እኤአ በአቴንስ ኦሎምፒክ ሲሆን በተመሳሳይ 5 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ 2008 ቤጂንግ ላይ አስመዝግባ 2012 ለንደን ደግሞ በኦሎምፒክ የተሳትፎ ታሪኳ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ 5 ሜትር አስመዝግባለች፡፡


ቲኪ ገላና
30ኛው የለንደን ኦሎምፒያድ 2012 አትሌት ፋጡማ ሮባ 16 ዓመታት በፊት በአትላንታ ኦሎምፒክ ያስመዘገበችውን ታሪክ በመድገም ለሁለተኛ ጊዜ በሴቶች ሁለተኛውን የማራቶን የወርቅ ሜዳልያ የተጎናኘፈች ናት፡፡
በለንደን ኦሎምፒክ ቲኪ ገላና በማራቶን አሸንፋ የወርቅ ሜዳልያ የተጎናፀፈችው አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዝገብ ጭምር ነው፡፡

 


አልማዝ አያና
ትውልዷ በቤንሻንጉል ጉምዝ ነው፡፡በብራዚል ሪዮ ዲጄኔሮ በተካሄደው 31ኛው ኦሎምፒያድ 10 ሜትር ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ወስዳለች፡፡ ያስመዘገበችው ሰዓት 2917.45 አዲስ የዓለም ሪከርድ ነው፡፡
23 ዓመታት በቻይናዊ አትሌት ተይዞ የነበረውን ሰዓት 14 ሰከንዶች ያሻሻለ ነው፡፡ በዚያው 31ኛው ኦሎምፒያድ ላይ   በተጨማሪ 5 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡



55 ሜዳልያዎች ከዓለም 41
በወንዶች
12 የወርቅ፣ 6 የብርና 12 የነሀስ ሜዳሊያዎች 4 ደረጃዎች 9 5 ደረጃዎች 3 እና 8 ደረጃዎች 30
1-5 ደረጃ ውጤች 30 ነጥብ - ከዓለም 17
በሴቶች
10 የወርቅ፣ 5 የብርና 9 የነሐስ ሜዳሊያዎች
4 ደረጃዎች 8 5 ደረጃዎች 5 6 ደረጃዎች 1 7 ደረጃዎች 3 እና 8 ደረጃዎች 2
1-3 ደረጃ ውጤቶች 24 ነጥብ - ከዓለም 11 55 የኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ሜዳልያዎች 31 ኦሎምፒያዶች ተካሂደዋል፡፡ 

 ኢትዮጵያ 13 ተሳትፋለች 12 የወርቅ፣ 11 የብር እና 21 የነሐስ ሜዳሊያዎች፤  4 ደረጃዎች 17 5 ደረጃዎች 8 6 ደረጃዎች 11 7 ደረጃዎች 6 እና 8 ደረጃዎች


 
የኦሎምፒክ ሪከርዶች
በኦሎምፒክ መድረክ በወንዶች  5 ሜትር እና 10 ሜትር ሁለት ክብረወሰኖችን የያዘው  ቀነኒሳ በቀለ ነው፡፡ ቀነኒሳ በቀለ ሁለቱንም የኦሎምፒክ ክብረወሰኖች እኤአ 2008 በቤጂንግ በተካሄደው 29ኛው ኦሎምፒያድ ሲያስመዘገባቸው 5 ሜትር 12 ደቂቃ 57.82 ሰኮንዶች እንዲሁም 10 ሜትር 27 ደቂቃ 04.7 ሰኮንዶች የሰፈሩ ናቸው፡፡
ኬንያውያን 800 1500 3 መሰናክልና በማራቶን የተያዙ የኦሎምፒክ ሪከርዶችን በመቆናጠጥ የተሻለ ውክልና አላቸው፡፡ በኦሎምፒክ መድረክ በሴቶች ምድብ በተመዘገቡ ሪከርዶች ኢትዮጵያ በሁለት አትሌቶች ስትጠቀስ ኬንያ ግን አንድም አላስመዘገበችም፡፡
በኢትዮጵያውያን የተያዙት ሁለት የረጅም ርቀት የኦሎምፒክ ሪከርዶች 2016 እእአ ላይ በሪዩዲጄኔሮ ኦሎምፒክ አትሌት አልማዝ አያና 10 ሜትር  29 ደቂቃ 17.45 ሰኮንዶች በሆነ ጊዜ ያስመዘገበችውና 2012 እኤአ ላይ በለንደን በተካሄደው 30ኛው ኦሎምፒያድ ቲኪ ገላና በማራቶን ስታሸንፍ ርቀቱን የሸፈነችበት 2 ሰዓት 23 ደቂቃ 07 ሰኮንዶች፡፡

***   ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***   ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***
 

ንጭ :-- ኦሎምፒክና የኢትዮጵያ ወርቃማ ኦሎምፒያኖች - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news