ከደራሲያን ዓምባ

Wednesday, August 4, 2021

ኢትዮጵያና ኦሎምፒክ

 ኦሎምፒክና የኢትዮጵያ ወርቃማ ኦሎምፒያኖች_ግሩም ሠይፉ( አዲስ )

 


1896 እኤአ ላይ የግሪኳ አቴንስ ከተማ ካስተናገደችው የመጀመርያው ኦሎምፒድ አንስቶ ባለፉት 125 ዓመታት ውስጥ በተካሄዱት 31 ኦሎምፒያዶች ኢትዮጵያ 13 ተሳትፋለች፡፡ በኦሎምፒክ መድረክ ሁሉንም ሜዳልያዎችን የሰበሰበችው በአትሌቲክስ ስፖርት ብቻ ሲሆን በከፍተኛ የውጤት ታሪካቸው ከሚጠቀሱ 8 አገራት አንዷ ናት። አፍሪካን በመወከል ደግሞ ከኬንያ ቀጥሎ ከፍተኛውን ስኬት አስመዝግባለች፡፡
የጃፓኗ ቶኪዮ ከምታስተናግደው 2020 32ኛው ኦሎምፒያድ በፊት ኢትዮጵያ በተካፈለችባቸው 12 ኦሎምፒያዶች 227 ኦሎምፒያኖች (168 ወንድ እና 59 ሴትተሳትፈዋል፡፡ ከእነሱም መካከል 32 ኦሎምፒያኖች 1 እስከ 3 ባሉ ደረጃዎች ስኬታማ በመሆን 54 ሜዳልያዎችን (22 የወርቅ፤ 11 የብርና 21 የነሐስ) ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል፡፡
ከሜዳልያዎቹ ስብስብ 22 የወርቅ ሜዳልያዎችን ለኢትዮጵያ ያጎናፀፉት 13 ኦሎምፒያኖች ናቸው፡፡ በተረፈ 11 የብር ሜዳልያዎች 10  እንዲሁም 21 የነሐስ ሜዳልያዎች 18 የኢትዮጵያ ኦሎምፒያኖች ተገኝተዋል፡፡

የወርቅ ሜዳልያ ክብርና ዋጋ
ኦሎምፒክ የዓለም አገራትና ህዝቦቻቸውን በአንድ መንፈስ የሚያስተባብር መድረክ ነው፡፡ በስፖርት መድረኩ በድህነት የተጎሳቆሉ፤ በበቂ የስፖርት መሰረተ ልማት ዝግጅታቸውን ያላከናወኑ፤ በየአገራቸው ባሉ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች የተረበሹ፤ በጦርነት እና በኢኮኖሚ ቀውስ የሚገኙ አገሮቻቸውን የወከሉ ኦሎምፒያኖች ሲሳተፉ ሁሉም አንድ ዓላማ ይኖራቸዋል፡፡ ይህ ዓላማ በሜዳልያ ክብር አገራቸውን ማኩራትና ሰንደቅ አለማቸውን ማውለብለብ ነው፡፡ የኦሎምፒክ የሜዳልያ ክብር መጎናፀፍ  ደግሞ የየትኛውም የዓለም ስፖርተኛ ህልም እንደሆነ ይታወቃል።
በኦሎምፒክ ታሪክ ሙሉ ለሙሉ ከወርቅ የተሰሩ ሜዳልያዎች ለአሸናፊዎች ለመጨረሻ ግዜ የተሰጠው 1912 እኤአ ላይ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ የኦሎምፒክ ሜዳልያዎች ገፅታ በአዘጋጅ አገራት የዲዛይን ፍላጎት እንዲሆን ቢፈቀድም ሜዳልያዎኙ የሚሰሩበት ማእድን በኦሎምፒክ ቻርተር መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል፡፡ በኦሎምፒክ 1 እና ሁለተኛ ደረጃ የሚሸለሙት የወርቅና የብር ሜዳልያዎች 92.5 በመቶ የሚሰሩት ከብር  እንዲሁም 6 በመቶ ከመዳብ ነው፡፡
3 ደረጃ ተሸላሚዎች የሚሰጡት የነሐስ ሜዳልያዎ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ከነሐስ የተሰሩ ናቸው፡፡ የወርቅ ሜዳሊያዎች 6 ግራም ወርቅ መለበጣቸው ግድ ነው፡፡ ሁሉም ሜዳልያዎች ውፍረታቸው 3ሚሜ  ዲያሜትራቸው 60 ሚሜ መሆን አለበት፡፡ አንድ የወርቅ ሜዳልያን አቅልጦ ይሸጥ ቢባል 706 ዶላር ጀምሮ ዋጋ ይኖረዋል፡፡
30ኛው ኦሎምፒያድ 4700 ሜዳልያዎች ለተሸላሚዎች የተዘጋጁ ሲሆን በሜዳልያዎቹ ስራ 802 ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡  ለኦሎምፒክ ሻምፒዮኖች የቀረቡ 302 የወርቅ ሜዳልያዎች 400 ግራም ይመዝናሉ፡፡


አበበ ቢቂላ
ትውልዱ ደብረብርሃን አቅራቢያ ጃቶ በተባለች ቦታ ነበር፡፡ 1960 እኤአ 83 አገራት የተውጣጡ 5 በላይ አትሌቶች በተካፈሉበት የሮም ኦሎምፒክ ላይ ለአፍሪካ እና ለኢትዮጰያ በኦሎምፒክ ታሪክ የመጀመርያውን ሜዳሊያ በማስገኘት ፈርቀዳጅ ታሪክ ሰርቷል፡፡  በባዶ እግሩ  ሮጦ ታላቁን የኦሎምፒክ ማራቶን በአንደኝነት ከማሸነፉም በተጨማሪ፤ 2162 በሆነ ሰአት አዲስ የአለም ሪከርድ አስመዝግቦም ነበር፡፡  
4 ዓመታት በኋላ 1964 እኤአ የኦሎምፒክ አዘጋጅ የጃፓኗ ከተማ ቶኪዮ ነበረች፡፡ የቶኪዮ ኦሎምፒክ 6 ሳምንታት ሲቀሩት፤ አበበ ቢቂላ የቀዶ ህክምና ተደርገለት። በፍጥነት እንደሚያገግም ተስፋ በማድረግ፤ የኦሎምፒክ ቡድን ውስጥ መካተቱ አልቀረም፡፡
ከቀዶ ጥገናው ሙሉ ለሙሉ ሳያገግም ማራቶኑን በመሮጥ በድጋሚ የኦሎምፒክ ሻምፒዮን ሆኖ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበ፡፡ ድሉ ለኢትዮጵያ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ብቻ አልነበረም  በድጋሚ የዓለም  ማራቶንን ሪከርድ አሻሽሏል - 21211 በሆነ ሰአት በመግባት፡፡ በሁለት ኦሎምፒኮች  በማራቶን አከታትሎ  በማሸነፍ፤ በሁለቱም ሪከርድ በማስመዝገብ እና ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎች በማግኘት፤ አበበ ብቸኛው ኦሎምፒያን ነው፡፡

ማሞ ወልዴ
ማሞ ወልዴ የተወለደው ከአዲስ አበባ 60 .. ርቀት ድሪጂሌ በተባለች የገጠር ከተማ ተወልዷል፡፡ ከአበበ ቢቂላ በኋላ የኢትዮጵያ ብቸኛ ተስፋ አንተ ብቻ ነህ ተብሎ 1968 እኤአ ላይ የሜክሲኮን ኦሎምፒክ የተሳተፈ ነበር፡፡
በሜክሲኮ ኦሎምፒክ 10 ሜትር ውድድር ኢትዮጲያን ወክሎ እንዲሮጥ የተመረጠው አትሌት ማሞ፤ ከከባድ ተቀናቃኞች ጋር ተፎካክሮ በአጨራረስ ብልሃት ስላልነበረው  ውድድሩን በሁለተኛነት ጨርሶ፤ በኦሎምፒክ ተሳትፎው ለራሱ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ተጎናፅፏል፡፡
 ማሞ ወልዴ 10 ሜትር የብር ሜዳልያው ድል በኋላ ግን ከዚህ አድካሚ ውድድር እፎይ የሚልበት ጊዜ አልነበረውም፤ በማራቶን እንዲወዳደርና የአበበን የድል ታሪክ መድገም እንደሚኖርበት የኢትዮጲያን ክብር የማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት በወቅቱ አሰልጣኝ የነበሩት አሰልጣኝ ንጉሴ ሮባ ተነገረው፡፡ 10 ሜትር ተወዳድሮ የብር ሜዳልያ ባገኘ በማግስቱ ነበር ማራቶኑ፡፡ ለመፎካከር ከተሰለፉት 44 አገራት አትሌቶች ውስጥ፤ ከኢትዮጲያ አበበ ቢቂላ፤ ማሞ ወልዴና ደሞሴ ነበሩበት፡፡ 15 ኪሎ ሜትር  ያህል  ሲመራ የቆየው የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ በህመም ውድድሩን አቋርጦ ለመውጣት ተገደደ፡፡ የስፖርት አፍቃሪዎች ልብ በሃዘን ተሰበረ፡፡  ጀግና ጀግናን እንደሚተካ የተዘነጋ ይመስላል፡፡  
በአበበ ቢቂላ በተከታታይ ሁለት ኦሎምፒክ ድል የተገኘበትን የማራቶን ውድድር ማሞ ወልዴ በድጋሚ አሸንፎ ታሪክ በመስራት የኢትዮጵያን ክብር አስጠበቀ፡፡ 35 አመቱ በአንድ ኦሎምፒክ ሁለት ሜዳሊያ ያጠለቀው ማሞ፤ ጀግንነቱ ለኢትዮጵያውን ኩራትንና ደስታን አጎናፀፈ፡፡ ከዚህ ስኬቱ በኃላ አትሌት ማሞ ወልዴ 1965 በጀርመን ሙኒክ በተካሄደው ኦሎምፒክ 10 ሜትር ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡


ምሩፅ ይፍጠር
ምሩፅ ይፍጠር በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ውስጥ በአዲግራት ተወለደ፡፡ በወጣትነቱ ከጋሪ ነጂ ጀምሮ፤ በተለያዩ ፋብሪካዎች ተቀጥሮ ሰርቷል፡፡
ለመጀመርያ ጊዜ በኦሎምፒክ የተሳተፈው የጀርመኗ ከተማ ሙኒክ ባስተናገደችው ኦሎምፒክ ሲሆን በአስር ሜትር ሶስተኛ ወጥቶ የነሃስ ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡በ1980 እኤአ የራሽያ ዋና ከተማ ያስተናገደችው የሞስኮ ኦሎምፒክ የምሩፅ ነበር፤ አለምን ጉድ ያሰኘበት፡፡ በሞስኮ ኦሎምፒክ 10ሺና 5 ሜትር ኢትዮጵያን በመወከል የተወዳደረው ምሩፅ፤  በፍፁም ብቃት በሁለቱም በማሸነፍ ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎችን ያገኘ ሲሆን በሁለቱም ርቀቶች በኦሎምፒክ ያሸነፈ የመጀመርያው አትሌት ነበር፡፡



ደራርቱ ቱሉ
ደራርቱ ቱሉ ትውልዷ በአርሲዋ ትንሽ ከተማ በቆጂ ነው፡፡  አትሌት ደራርቱ ቱሉ ለኢትዮጲያዊያን ብቻ ሳይሆነ ለአፍሪካዊያን እንስት አትሌቶች ፈርቀዳጅ የሆኑ ድሎችን በአለም አቀፍ ደረጃ ታሪክ ሠርታለች፡፡
በተለይ ደግሞ የሚጠቀሰው  1992 .. በስፔን ባርሴሎና በተከናወነው ኦሎምፒክ  10 ሜትር የወርቅ ሜዳልያ መጎናፀፏ ነው፡፡ ይህ ድል በአፍሪካ የኦሎምፒክ ታሪክ በረጅም ርቀት በሴቶች የመጀመርያው ድል ነበር። 2000 እኤአ በአውስትራያ በተካሄደው የሲድኒ ኦሎምፒክም ደራርቱ 10 ሜትር ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለመጎናፀፍ በቅታለች፡፡ በተጨማሪም 2004 እኤአ በአቴንስ ኦሎምፒክ 10 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡

 




ፋጡማ ሮባ
አትሌት ፋጡማ ሮባ  የተወለደችው በአርሲዋ በቆጂ ከተማ ነው፡፡ 1996 .. ላይ የአሜሪካዋ አትላንታ ባስተናገደችው ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን በታሪክ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ለኢትዮ ለመጎናፀፍ በቅታለች፡፡

 


 ኃይሌ ገብረስላሴ
ትውልዱ በአርሲዋ ትንሽ ከተማ በቆጂ ነው። ኃይሌ /ሥላሴ ለመጀመርያ ጊዜ 1996 .. ላይ በአትላንታ ኦሎምፒክ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ በመሳተፍ 10 ሜትር ውድድር ተካፍሎ በአስደናቂ የአጨራረስ ብቃት በማሸነፍ የመጀመሪያውን የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል፡፡
2000 .. ላይ 20ኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ ኦሎምፒክ በአውስትራሊያ ሲድኒ ከተማ ሲካሄድ ኃይሌ 10 ሜትር በተካሄደው ውድድር  ከቅርብ ተቀናቃኙ የኬንያው አትሌት ፖልቴርጋት ጋር ያደረገው እልህ አጨራረስ ትንቅንቅ 0.09 ሰኮንድ ልዩነት በመቅደም 2ኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለመጎናፀፍ በቅቷል፡፡

 


ሚሊዩን ወልዴ
አትሌት ሚሊዩን ወልዴ ትውልዱ በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ 2000 .. በአውሰትራሊያ ሲዲኒ በተከናውነው 27ኛው ኦሎምፒያድ አዲስ እና ፈርቀዳጅ ታሪክ ለኢትዮጰያ አትሌቲክስ በማስመዝገብ ተሳክቶለታል፡፡  
በወቅቱ 22 ዓመት ወጣት የነበረው አትሌት ሚልዩን በተካፈለበት 5 ሜትር ውድድር አሸንፎ በርቀቱ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ሲያስመዘግብ በመጨረሻዎቹ 200 ሜትሮች ድንቅ የአጨራረስ ብቃት በማሳየት  ነበር፡፡


ገዛሐኝ አበራ

የአትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው አርሲ የተወለደው ገዛሐኝ በኢትዮጲያ የኦሎምፒክ ተሳትፎ ታሪክ ማሞ ወልዴ ካስመዘገበው የወርቅ ሜዳልያ በኋላ በማራቶን ሊያሽንፍ የበቃ አትሌት ነው፡፡
2000 እኤአ በሲዲኒ ኦሎምፒክ ላይ ገዛሐኝ በማራቶን የወርቅ ሜዳልያውን ሊጎናፀፍ የበቃ ሲሆን  22 ዓመቱ በኦሎምፒክ ታሪክ የመጀመሪያው ወጣት የማራቶን ባለድል ለመሆን ፈርቀዳጅ ታሪክ ለመስራት የቻለበት ነበር፡፡



ቀነኒሳ በቀለ
ትውልዱ በአርሲ በቆጂ የሆነው ቀነኒሳ 10 ሜትር ሶስት ጊዜ 5 ሜትር አንድ ጊዜ በአጠቃላይ 4 የኦሎምፒክ የወርቅ እንዲሁም በሺ ሜትር 1 የብር ሜዳልያዎችን በተጨማሪ በማስመዝገብ በወንድ አትሌቶች በኦሎምፒክ መድረክ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበ ነው፡፡
ቀነኒሳ በኦሎምፒክ መድረክ የመጀመርያ ተሳትፎው 28ኛው ኦሎምፒያድ በግሪክ አቴንስ ላይ የነበረ ሲሆን፤  አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዘገብ ለራሱ የመጀመርያውን የወርቅ ሜዳልያ ለማጥለቅ በቃ፡፡ በወንዶች 5 ሜትር ደግሞ የብር ሜዳልያ ነበረው፡፡
4 ዓመታት በኋላ የቻይናዋ ዋና ከተማ ባስተናገደችው 29ኛው ኦሎፒያድ በድጋሚ አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዝገብ 10 ሜትር የሻምፒዮናነት ክብሩን አስጠብቆ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ሊያገኝ የበቃ ሲሆን 5 ሜትርም ድል በማድረግ ሌላ የወርቅ ሜዳልያውንም ተጎናፅፏል፡፡ 1980 እኤአ ላይ በሞስኮ ኦሎምፒክ አትሌት ምሩፅ ይፍጠር  5ሺና 10 ድርብ ድል በማግኘት ያስመዘገበውን ታሪክ በመድገምም አስደናቂ ታሪክ ሊሰራ በቅቷል፡፡ 2012 እኤአ ለየእንግሊዟ ከተማ ለንደን ባስተናገደችው 30ኛው ኦሎምፒያድ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 10 ሜትር ለሶስትኛ ጊዜ የወርቅ ሜዳልያ በመጎናፀፍ በታሪክ የመጀመርያው አትሌት ሆኖ አዲስ ታሪክም ሊያስመዘግብ በቅቷል፡፡


ጥሩነሸ ዲባባ
ትውልዷ አርሲ ውስጥ በቆጂ አጠገብ በምትገኝ ጨፌ በተባለች ስፍራ ነው፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ በኢትዮጲያ የኦሎምፒክ ተሳትፎ ታሪክ በሁለቱም ፆታዎች  እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛው የውጤት ክብረወሰን በማስመዝገብ በግንባርቀደምነት ትጠቀሳለች፡፡
ጥሩነሽ ዲባባ በተሳተፈችባቸውየኦሎምፒክ መድረኮች  2004 እኤአ በአቴንስ፤ 2008 እኤአ በቤጂንግ እንዲሁም 2012 እኤአ በለንደን 5 (3 የወርቅና ሁለት የነሐስ) ሜዳልያዎችን በማግኘት ከረጅም ርቀት አትሌቶች በአንደኛ ደረጃ የከፍተኛ ውጤት ክብረወሰን ይዛለች፡፡
እነዚህ ሜዳልያዎች ላይ 5 ሜትር ነሐስ 2004 አቴንስ ላይ፤  10 እና 5 ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎች 2008 ቤጂንግ ላይ፤ እንዲሁም  10 ወርቅ እና 5 ነሐስ ሜዳልያዎች 2012 ለንደን ላይ ያገኘቻቸው ናቸው።
በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ 5 የወርቅ እና ሜዳልያዎች በመሰብሰብ በረጅም ርቀት ብቸኛውን የውጤት ክብረወሰን እንደያዘች ነው፡፡

 


መሰረት ደፋር
አትሌት መሰረት ደፋር ትውልዷ በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ በኦሎምፒክ የተሳትፎ ታሪክ 5 ሜትር ሴቶች ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎችን ያስመዘገበች ምርጥ አትሌት ናት፡፡
የመጀመርያ የወርቅ ሜዳልያዋን ያስመዘገበችው 2004 እኤአ በአቴንስ ኦሎምፒክ ሲሆን በተመሳሳይ 5 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ 2008 ቤጂንግ ላይ አስመዝግባ 2012 ለንደን ደግሞ በኦሎምፒክ የተሳትፎ ታሪኳ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ 5 ሜትር አስመዝግባለች፡፡


ቲኪ ገላና
30ኛው የለንደን ኦሎምፒያድ 2012 አትሌት ፋጡማ ሮባ 16 ዓመታት በፊት በአትላንታ ኦሎምፒክ ያስመዘገበችውን ታሪክ በመድገም ለሁለተኛ ጊዜ በሴቶች ሁለተኛውን የማራቶን የወርቅ ሜዳልያ የተጎናኘፈች ናት፡፡
በለንደን ኦሎምፒክ ቲኪ ገላና በማራቶን አሸንፋ የወርቅ ሜዳልያ የተጎናፀፈችው አዲስ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማስመዝገብ ጭምር ነው፡፡

 


አልማዝ አያና
ትውልዷ በቤንሻንጉል ጉምዝ ነው፡፡በብራዚል ሪዮ ዲጄኔሮ በተካሄደው 31ኛው ኦሎምፒያድ 10 ሜትር ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ወስዳለች፡፡ ያስመዘገበችው ሰዓት 2917.45 አዲስ የዓለም ሪከርድ ነው፡፡
23 ዓመታት በቻይናዊ አትሌት ተይዞ የነበረውን ሰዓት 14 ሰከንዶች ያሻሻለ ነው፡፡ በዚያው 31ኛው ኦሎምፒያድ ላይ   በተጨማሪ 5 ሜትር የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡



55 ሜዳልያዎች ከዓለም 41
በወንዶች
12 የወርቅ፣ 6 የብርና 12 የነሀስ ሜዳሊያዎች 4 ደረጃዎች 9 5 ደረጃዎች 3 እና 8 ደረጃዎች 30
1-5 ደረጃ ውጤች 30 ነጥብ - ከዓለም 17
በሴቶች
10 የወርቅ፣ 5 የብርና 9 የነሐስ ሜዳሊያዎች
4 ደረጃዎች 8 5 ደረጃዎች 5 6 ደረጃዎች 1 7 ደረጃዎች 3 እና 8 ደረጃዎች 2
1-3 ደረጃ ውጤቶች 24 ነጥብ - ከዓለም 11 55 የኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ሜዳልያዎች 31 ኦሎምፒያዶች ተካሂደዋል፡፡ 

 ኢትዮጵያ 13 ተሳትፋለች 12 የወርቅ፣ 11 የብር እና 21 የነሐስ ሜዳሊያዎች፤  4 ደረጃዎች 17 5 ደረጃዎች 8 6 ደረጃዎች 11 7 ደረጃዎች 6 እና 8 ደረጃዎች


 
የኦሎምፒክ ሪከርዶች
በኦሎምፒክ መድረክ በወንዶች  5 ሜትር እና 10 ሜትር ሁለት ክብረወሰኖችን የያዘው  ቀነኒሳ በቀለ ነው፡፡ ቀነኒሳ በቀለ ሁለቱንም የኦሎምፒክ ክብረወሰኖች እኤአ 2008 በቤጂንግ በተካሄደው 29ኛው ኦሎምፒያድ ሲያስመዘገባቸው 5 ሜትር 12 ደቂቃ 57.82 ሰኮንዶች እንዲሁም 10 ሜትር 27 ደቂቃ 04.7 ሰኮንዶች የሰፈሩ ናቸው፡፡
ኬንያውያን 800 1500 3 መሰናክልና በማራቶን የተያዙ የኦሎምፒክ ሪከርዶችን በመቆናጠጥ የተሻለ ውክልና አላቸው፡፡ በኦሎምፒክ መድረክ በሴቶች ምድብ በተመዘገቡ ሪከርዶች ኢትዮጵያ በሁለት አትሌቶች ስትጠቀስ ኬንያ ግን አንድም አላስመዘገበችም፡፡
በኢትዮጵያውያን የተያዙት ሁለት የረጅም ርቀት የኦሎምፒክ ሪከርዶች 2016 እእአ ላይ በሪዩዲጄኔሮ ኦሎምፒክ አትሌት አልማዝ አያና 10 ሜትር  29 ደቂቃ 17.45 ሰኮንዶች በሆነ ጊዜ ያስመዘገበችውና 2012 እኤአ ላይ በለንደን በተካሄደው 30ኛው ኦሎምፒያድ ቲኪ ገላና በማራቶን ስታሸንፍ ርቀቱን የሸፈነችበት 2 ሰዓት 23 ደቂቃ 07 ሰኮንዶች፡፡

***   ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***   ***  ***  ***  ***  ***  ***  ***
 

ንጭ :-- ኦሎምፒክና የኢትዮጵያ ወርቃማ ኦሎምፒያኖች - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news

Friday, July 30, 2021

ድምፀ-ነጎድጓዱ ጋዜጠኛ ታደሠ ሙሉነህ

ጋዜጠኛ ታደሠ ሙሉነህ (1938 ዓ.ም. - 2004 ዓ.ም.)
  • ድምፀ-ነጎድጓዱ ጋዜጠኛ
  • ድምፀ ሸጋው ጋዜጠኛ
  • ራሱ ታደሠ ሬድዮ ነው።
  • የኢትዮጵያ ሬድዮ የእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ጀማሪ
  • ጋሽ ታዴ ...

"ዜና እንደሙዚቃ ተደመጠ ማለት፣
 ታደሰ ተረኛ ሆኖ የገባ ዕለት።"       ጋዜጠኛ ንጉሴ አክሊሉ ጋሽ ታዴ  የተቀኝለት

 አንጋፋው ጋዜጠኛ ጋሽ ታደስ ሙሉነህ በሸገር ሬድዮ በትዝታ ዘአራዳ












Tuesday, May 18, 2021

ይህ የኢትዮጵያ ሬዲዮ ነው

 

“የሕዝቡን ዐይን በሬዲዮ እንክፈት” 

በሚል በፈር ቀዳጅነት የተተከለው የኢትዮጵያ ሬዲዮ፤ 

የ85ኛ ዓመት ሻማውን 
(መስከረም 2 ቀን 2013 ዓ.ም.) ለኮሰ።


 

በአሁኑ ወቅት ንፋስ ስልክ በሚል የምናውቀው አካባቢ ስሙን ያገኘው ሬዲዮ ለሚለው ቃል ሀገራዊ መጠሪያ ሲወጣለት በነፋስ የሚሄድ “ያለ ሽቦ ቃል የሚያሳልፍ መኪና” ተብሎ ከመሰየሙ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮ ታሪክ ከቴሌ ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ የቴክኒክ ሰራተኞቹ ቅጥር በቴሌ ስር ነበር፡፡ በቀደምቱ ጊዜ በኢትዮጵያ ሬዲዮ ለሚሰራ ጋዜጠኛ ትልቁ እድሉ ከአንጋፋዎቹና ነባሮቹ ጋር መካከለኛዎቹና አዲሶቹ ተጣምረው ስለሚሰሩ ደቀ መዝሙሮቹ ከመምህሮቹ የካበተ እውቀትና የተፈተነ ልምድ የሚቀስሙበት ሰፊ እድል ነበር፡፡ ጀማሪዎች ወደ ህዝብ ከመቅረባቸው በፊት በሙያ ተገርተው ተቃንተው እውቀትን ከክህሎተ በማዳበር የሙያ ስነ ምግባርን ከማህበራዊ ህይወት አዋዶ ለመማር የሚያግዝ ታላቅ ኮሌጅ ነው ብሎ ደፍሮ መናገር ይቻላል፡፡

ግርማዊ ቀዳማዊ ሀ/ስላሴ የማእዘን ድንጋይ በ1923 ሲያስቀምጡ “ያለሽቦ ቃል የሚያሳልፍ መኪና” ብለው ነበር ሬዲዮን የጠሩት፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮ የኢጣሊያ አንሶልዶ ኩባንያ በንፋስ ስልክ አካባቢ በሰራው ሬዲዮ ጣቢያ ስራውን መስከረም 2 / 1928 ጀምሮ ዛሬ ላይ 85ኛ አመቱን ሲያከብር የመጀመሪያዎቹ የሬዲዮ አንባቢዎች ከወንዶች ከበደ ሚካኤል ከሴቶቸ ደግሞ ወ/ሮ ሮማነወርቅ ካሳሁን ይጠቀሳሉ፡፡

ዲዮው ያኔ ከአ/አ ርቆ አለመሰማቱ ብቻ ሳይሆን ፉጨትና ይጮህም ስለነበር ጥራት ይጎድለዋል፡፡ ግርማዊነታቸው በነገሱና ሬዲዮውም በጀመረ አጭር ጊዜ ውስጥ ኢጣሊያዎች ጣቢያውን አስቀርተው የራሳቸውን ጣቢያ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ላይ መስርተው ዘመናዊ ትምህርት ያላቸውን ኢትዮጵያውያን አሳደው መግደልና የተረፉትንም ለራሳቸው ቢሮ ግልጋሎት እየነጠቁ ከተወሰዱት መካከል ብላታ ወ/ጊዮርጊስ ወ/ዮሀንስና ከበደ ሚካኤል ይጠቀሳሉ፡፡ ጣቢያውንም አፍሪካ ኦሪዬንታሌ ኢታልያና በማለት የኢጣሊያ ምስራቃዊ አፍሪካ ሬዲዮ በማለት በኢትዮጵያ _ በኤርትራና በሶማሊያ ሀገርን የሚያዳክም ፐሮፖጋንዳ ይሰራጭበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮም በ1933 ቀድሞ ወደነበረበት ንፋስ ስልክ አልተመለሰም፡፡

በይዘት ደረጃ ደግሞ ከ1950ዎቹ ወዲህ በእንግሊዝኛ ውጭ ተምረው የመጡት እነ ጋሽ ሉልሰገድ ኩምሳ ‘ ወ/ሮ እሌኒ መኩሪያ እና ሳሙኤል ፈረንጅ አይዘነጉም፡፡ ያኔ በሞጋችና በይዘት ጥልቅ ቅንብሮቻቸው ስመጥር ከነበሩት መካከል አሳምነው ገ/ወልድ ‘ በመምህሬ አብራራው መጠሪያ የሚታወቀው መንግስቱ መኮንን ‘የስፖርቱ ሰለሞን ተሰማ ‘ በአጠቃላይ ትንተን አሀዱ ሳቡሬና አቶ ነጋሽ ገ/ማርያም በሳይንስ ሻምበል አፈወርቅ ዮሀንስ ‘ ጳውሎስ ኞኞ ‘ በአሉ ግርማ እንዲሁም በጥበባት ደግሞ ዮሀንስ አድማሱ ‘ አብዬ መንግስቱ ለማ ‘ ሰአሊና ገጣሚ ገ/ክርስቶስ ደስታ ‘ ሰለሞን ደሬሳና ተስፋዬ ገሰሰ “የኪነ ጥበባት ጉዞ” የሚል ፕሮግራምን ያዘጋጁ ነበር፡፡

ያኔ በሬዲዮ ጅማሮው ወቅት የማስታወቂያ ሚኒስትር የነበሩት ድጃዝማች ግርማቸው ተ/ሀዋርያት በ1954 የአለም አቀፍ አገልግሎቱ ጅማሮ ሁነት ላይ፡_ “ከእንግዲህ ወዲህ ኢትዮጵያ ወዳጅ በሆኑት አፍሪቃ ‘መካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ የምትሰማ ይሆናል፡፡ ከአለም ህዝቦች ጋር ለመቀራረብም እንደሚረዳ የታመነ ነው ብለው ነበር፡፡

እኔ ከ1980ቹ አጋማሽ ወዲያ ከዩኒቨርስቲ ወጥቼ ከጥቂት ወራት መምህርነት ቀጥሎ ዜና ፋይልን ስቀላቀል ከአንጋፋዎቹ ጋሽ ጥላሁን በላይና ከጋሽ ዳሪዎስ ሞዲ አለቆቻችን አንስቶ ‘ የፈረቃ መሪዎች ከነበሩት እጅግ ነባሮቹ ዳንኤል ወ/ሚካኤል ‘ በቃሉ ደገፋው ‘ ንግስት ሰልፉ ‘ ዋጋዬ በቀለና ነጋሽ መሀመድ ነበሩ፡፡ በመቀጠል አሁንም ከነባሮቹ መካከል አማረ መላኩ ‘ ተካልኝ ይርሳው ‘እ/ህይወት ደምሴ ‘ ደበበ ዱፌራ ‘ ገነት አስማረ ‘ ተስፋዬ መክብብ ‘ አለምነህ ዋሴ ‘ ደስታ ሎሬንሶ ‘ብርትኩዋን ሀ/ወይን ‘ ተፈሪ አንለይ ‘ ተፈሪ ለገሰ ‘ ሺበሺ ጠጋዬና ቴዎድሮስ ነዋይ ሲወሱ በተከታይነትም እሸቱ ገለቱ ‘እሸቱ አበራ ‘እሸቱ አለሙ ‘ ስለሺ ሽብሩ ‘ ደግነህ ገ/ስላሴ ‘ ዘመድኩን ተክሌ ‘ ብሩከ ነጋሽ ‘ ታደሰ ዝናዬ’ አማኑኤል አብዲሳ ‘አዲስ አለማየሁ ‘ የኔነህ ከበደ ‘ አብዱልሰመድ መሀመድ ‘ቢኒያም ከበደ ‘ ለምለም በቀለ ‘ እያደር አዲስ ‘ዳንኤል አማረ ‘አለማየሁ ግርማ ‘ ሰለሞን ግዛው ‘ ሳሙኤል ፍቅሬ ‘ ሲሳይ ዘሪሁን ‘ ጌታሁን ንጋቱ ‘ ምናላቸው ስማቸው ‘ሀ/እየሱስ ወርቁና ጋሻው ተፈራ ነበሩ፡፡

ከዚህ ወዲያ ነበር እነ አሸናፊ ሊጋባ ‘ ነጣነት ፈለቀ ‘ አዲሱ መሸሻ ‘ ሰሎሜ ደስታ ‘ሰኢድ ሙሄ እና ሰለሞን ዮሀንስ የተቀላቀሉን፡፡ ከዜና ክፍል ጋር በስፖርቱ ጋሽ ይንበርበሩ ምትኬ ‘ ጎርፍነህ ይመር ‘ ደምሴ ዳምጤ ‘ ዳዊት ንጉሴ ‘ ዳንኤል ጋሻውና ታደለ ሲጠቀሱ ለፕሮግራም ስራ መስክ በወጡ ቁጥር ዜና ይዘው ከሚመጡት መካከል ደግሞ ሞገስ መኮንን ‘ አስቻለው ጌታቸው እና ነቢያት ገቢሳ አይዘነጉኝም፡፡

በኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ጥበባዊ ዝግጅቶችን በማቅረብም እነ ጋሽ ታደሰ ሙልነህ ‘ንጉሴ አክሊሉ ‘ አዲሱ አበበ ‘አባይነሽ ብሩ ‘ታምራት አሰፋ ‘ጠሀይ ተፈረደኝ ‘ደረጀ ሀይሌ ‘ዳንኤል አያሌው ‘ ጌታቸው ማንጉዳይ ‘ ቤዛዬ ግርማ ‘ ነጋሽ ግዛው ‘ሰለሞን ደስታ ‘ ሂሩት መለሰ ‘ደጀኔ ጥላሁን ‘ አስፋው ገረመው ‘ በልሁ ተረፈ ‘ ልባርጋቸው ሽፈራው ‘ብርሀኑ ገ/ማርያም ‘ ቅድስት በላይ ‘ መስፍን ዘለቀ ‘ አምባዬ አማረ ‘አስካለ ተስፋዬ ‘ ዘውዱ ግርማና መሳይ አለማየሁ ሲሆኑ ከብሄራዊ ሬዲዮ አገልግሎቱ የተዛወሩትንም ለአብነት እንዳልካቸው ፈቃደ ‘ አስቻለው ሽፈራው ‘ ኤልሳቤት ሳሙኤል ‘ ማርታ ጠጋውና አበበ ፈለቀ ሊነሱ ይችላሉ፡፡

ከ1956 ወዲህ ሰፋ ያለ አካባቢን የሚሸፍን በ9 ቦታዎች ማሰራጫ በመትከል ለማሻሻል ታስቦ በገንዘብ ውሱንነትን የየአካባቢው የፖለቲካ ሽፍታ በትንሽ መሳሪያ ጣቢያውን በመቆጣጠር ንጉስ ሆኛለሁ እያለ ስጋት እንዳይጭር በሚል በ3 ቦታ ብቻ ተወስኖ በአዲስ አበባ ጌጃ ዴራ _ በአስመራ አዲ ኡግሪ እንዲሁም በሀረር ሀኪም ጋራ ላይ ተተከለ፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮ የማሰራጫ አድማሱን በማስፋት ከ1984 ወዲህ የመቱ ማሰራጫ አኙዋክና ኑዌርን ከጨመረ አንስቶ በ11 የመግባቢያ መንገዶች መረጃዎችን ለህዝብ እያቀበለ እንደቀጠለ ነው፡፡ ከ1959 ወዲያ ግርማዊነታቸው በ35ኛው የዘውድ በአላቸው ሰፊ ሽፋን ያለውን ማሰራጫ አስመርቀው የአዲስ አበባ ብቻ በሚል ይጠራ የነበረው የኢትዮጵያ ለመባል በቃ፡፡

በተማከለ መልኩ የሬዲዮ ዜና ማእከል ሁሉንም ዴስኮች ካሰባሰበ ወዲያ ከኦሮምኛ እነ ጋሽ ተስፋዬ ቱጂ ‘ ሀሊማ ኢብራሂም’ ዮሀንስ ዋቆ ‘ፉሪ ቦንሳ ‘ ጋሸ አለማየሁ ‘ ጋሽ ሁሴን ‘በዳሶ ሀጂ ‘ መክብብ ሸዋ ‘ኢሳ ኡመር ‘ ካሳሁን ፈይሳ ‘ራሄል ግርማ ከብዙ በጥቂቱ ሲታወሱ ከትግርኛ ደግሞ እነ ነጋ ‘ተወልደ ‘ ኪሮስ ‘እዮብ ‘ ብርሀነ ‘ትርሀስ ‘ አማን አሊ ‘ ገ/አምላክ ተካ ‘ አክሊሉ ደባልቀው ‘ አሰፋ በቀለ ‘አልማዝ በየነና ዮናስ አይዘነጉም፡፡

ከአንግሊዝኛ ዴስክ ጋዜጠኞች እነ ጋሽ ዮሀንስ ወ/ሩፋኤል ‘ ግሩም ታሪኩ ‘ መለሰ ኢዳ ‘ስለሺ ዳቢ ‘ ባህሩ ተመስገን ‘ፍ/ህይወት ‘ ንግስት ‘ቴዎድሮስ ዘውዴ ‘ ሲሳይ ሀ/ስላሴ ‘ ብሩኬ ከብዙ በጥቂቱ ሲነሱ ከፈረንሳይኛ እነ ጋሽ ጌታቸው ተድላ ‘ ጋሽ ፍራንሲስ ‘ጋሽ ተስፋዬ ‘ ርብቃን እናውሳና ከአረብኛ እነ ጋሽ አደም ኡስማን ‘ሼህ ኢብራሂም ‘ ጋሽ መኮንን ‘ ከድርና ካውሰር ይጠቀሳሉ፡፡ ከሶማሊኛ ጋሽ ጊሬ ‘ ሀሰን እና አብዱላሂን ሳንዘነጋ አፋር ዴስክ ጋ ስንሻገር እነ አብዲና አህመድን ሳንጠቅስ አናልፍም፡፡

ከ1990ዎቹ ወዲያ የመጡትን ደግሞ ከአሸናፊ ሊጋባ በከፊል ወስጄ የሚከተሉትን ለመጥቀስ ያህል ብሩክ ያሬድ ፣ አብዲ ከማል ፣ የትምወርቅ ዘለቀ ፣ ፍትሃወቅ የወንድወሰን ፣ ሀና ተሟሪ ፣ ፋሲል ግርማ ፣ ህይወት ደገፉ ፣ መሰረት ተመስገን ፣ እያሱ ፈጠነ ፣ ሰለሞን ገዳ ፣ ሰይፉ ገብረጻድቅ ፣ እየሩሳሌም ተክለጻዲቅና ሌሎችንም እናንተው አክሉበት፡፡

በመዝናኛው ዛሬ ላይ የሸገር ሬዲዮ ባለቤት የሆኑት እነ መአዛ ብሩና ተፈሪ አለሙ _ የኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ታላቅ ባለድርሻዎች በአብዬ ዘርጋው የሚታወቀው ሰራዊት ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁን እንዲሁም የአሻም ቲቪ ባለድርሻዎቹ እነ ሱራፌል ወንድሙ ‘ ግሩም ዘነበ ብሎም በግዞ ተከታታይ የሬዲዮ ድራማ መለያው የነበረው የባላገሩ ቲቪ ባለድርሻው አብረሃም ወልዴ _ እነ አብረሀም አስመላሽና እከ ንብረት ገላውን ጨምሮ በኢትዮጵያ ሬዲዮ ስራቸው ለምልሞ ያደጉ ናቸው፡፡ በሀገር ቤትና ውጭ ያሉና የነበሩ እነ አሸናፊ ዘደቡብ ‘እሸቴ ከጃን ሜዳ ‘ ዳንዴው ሰርቤሎ ‘ ቀስቶ ከኮተቤ ‘እነ ሀይሉ ጠጋዬ ‘ ተመስገን አፈወርቅ ብቻ ማንን ጠቅሼ ማንን ልተው የዘለልኩትን አክሉበት፡፡

ከቴክኒክ ክፍሉ ከእነ ጋሽ ተካ ወ/ሀዋርያት ‘ ጋሸ ገበየሁ ኑሬሳ ‘ መቅደስ አማረ ‘ ትርሲት ወንድሙ ‘ አቢ ‘ ይትባረክ ‘የአይኔአበባ ተክሌ ‘ በለጥሻቸው ‘ ሰላማዊትና ቤቲ ከብዙ በጥቂቱ እንዲሁም ከማሰራጫ ጋሸ ከበደ ጎበና ‘ጋሽ መላከ ‘ ኢ/ር ዘገየ ‘ጋሽ ካሳ ሚልኮ ‘ ሲሳይ ‘ክንዱ ‘ዘሪሁን ‘ ገረመው ‘ ተስፋዬ ‘ዳዊት ‘ ለዊ በተጨማሪነትም በሞኒተሪንግና ታይፕ እነ ሙሉ ‘ገነት ‘ ቆንጂት ‘ታየች ‘ጥሩዬና ሰናይት ‘ መስፍኔ ‘አስኒ ‘ ብዙዬ እና አሰለፍ አይረሱኝም፡፡

ያኔ ከወረራው ወዲህ በ1934 ኢትዮጵያ ሬዲዮ ተመልሶ እንደገና በቀን የ4 እና 5 ሰአት የቀጥታ ስርጭቱን ሲቀጥል 3 አላማዎች ነበሩት፡፡ ያኔ በጃንሆይ በድልድሉ መሰረት . . . 1 _ ዜናን ኢንፎርማሊያን . . . 2 _ ትምህርታዊ ኢጂኬሽን . . . 3 _ አዝናኝ ኢንተርቴይንመንት ሆነው በምጣኔ ረገድ 60 በመቶው አሳዋቂና አስተማሪ መሆን ሲጠበቅባቸው ቀሪ 40 በመቶው እጅ ደግሞ ለመዝናኛ እንዲሆን ተወስኖ ነበር፡፡ (*የጋዜጠኛ እሸቱ ገለቱ ጽሑፍ)


የኢትዮጵያ ሬዲዮ ትዝታ: በ አርትስ ቲቪ በነገራችን ላይ ክፍል _፩ 

የኢትዮጵያ ሬዲዮ ትዝታ: በ አርትስ ቲቪ በነገራችን ላይ ክፍል _፪

የኢትዮጵያ ሬዲዮ ትዝታ: በ አርትስ ቲቪ በነገራችን ላይ ክፍል _፫




 




Monday, May 3, 2021

ሚሻ ሚሾ (ሙሾ)

 


 ከበዓለ ስቅለት ባህላዊ መገለጫዎች አንዱ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚዘወተረው ‹‹ሚሻ ሙሾ›› ነው፡፡

ስለዚህ ባህላዊና ትውፊታዊ ሥርዓት ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ መታፈሪያ ‹‹መዝገበ በረከት ዘሰሙን ቅድስት›› በተሰኘውና መሰንበቻውን ለንባብ በበቃው መጽሐፋቸው ዘርዘር አድርገው ማስረጃዎች እያጣቀሱ አቅርበውታል፡፡

በደራሲው አገላለጽ፣ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ወንዶች ሕፃናት ደግሞ ‹‹ሚሻ ሙሾ›› እያሉ እየዘመሩ በየቤቱ እየዞሩ ዱቄት ይለምናሉ፡፡ በዓሉ በቂጣ ስለሚከበር የአይሁድ የቂጣ በዓልን ይመስላል፡፡ አለቃ ታየ ገብረ ማርያም በ1902 ዓ.ም. በታተመው የትብብር ሥራቸው ‹‹ሚሻ ሚሾ›› የሚለው ስያሜ የት መጣ ‹‹ውሾ ውሾ›› ከሚል እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡

ሊቀ ሥልጣናት አባ ሀብተ ማርያም ወርቅነህ ‹‹ማኅበራዊ ኑሮ በኢትዮጵያ›› ብለው በሰየሙት መጽሐፋቸው፣ ይህም አይሁድን ለመስደብ የተሰነዘረ እንደሚመስል ይገልጻሉ፡፡ በሌላ መልኩ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ደግሞ ‹‹ሚሻ ሚሾ›› ወዲያ ወዲህ፣ ከዚያ ከዚህ ማለት ነው፡፡ ይህም ከየቤቱ ዱቄቱ የሚሰበሰብ መሆኑን ለማመልከት ነው በማለት ያስረዳሉ፡፡ በተጨማሪም የትውፊቱ ትክክለኛ መጠሪያ ‹‹ሙሾ ሙሾ›› የክርስቶስን ሕማም ለመግለጽ የተሰጠ መሆኑን፣ በጊዜ ሒደት ተለውጦ ‹‹ሚሻ ምሾ›› መባሉንም ይገልጻሉ፡፡

አለቃ ደስታ ተክለ ወልድም የቃሉን ፍች ‹‹ሙሾ (ምሾ) የለቅሶ ዜማ፣ የለቅሶ ቅንቀና፣ ግጥም፣ ዜማ፣ ቁዘማ፣ እንጉርጎሮ፣ ረገዳ፣ ጭብጨባ ያለበት›› በማለት ያስረዳሉ፡፡ ይኼኛው ሐተታ ከክዋኔው ጋር ቀጥታ ቁርኝት አለው፡፡ ሕፃናቱ በየቤቱ መሄዳቸው አይሁድ ሐሙስ ሌሊት ከሐና ወደ ቀያፋ፣ ከቀያፋ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤት መዞራቸውን ለመዘከር ነው፡፡ ሕፃናት ይህን ዕለት እንዲያስታውሱት በየዓመቱ እንዲዘክሩ በማድረግ ይቻል ዘንድ ሊቃውንት ይህንን ሥርዓት እንደሠሩ ይናገራሉ፡፡

‹‹ሕፃናት ከምሴተ ሐሙስ ጀምረው እስከ በዓለ ስቅለት ምሽት የሚሻ ሙሾን ዝማሬ እያሰሙ በየቤቱ በመዞር ዱቄት የሚያሰባስቡት ትውፊታዊ ክዋኔ አለው፡፡ ሕፃናቱ በየቤቱ ዱቄት ለመሰብሰብ ሲዞሩ በቀለማት ወይም በእሳት ተለብልቦ የተዥጎረጎረ ቀጭን ዘንግ ይይዛሉ፡፡ መሬቱን በዘንግ በመምታት ዱቄት እስኪሰጣቸው ድረስ በተለያዩ ግጥሞች የታጀበ ዝማሬ ያሰማሉ፡፡ ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዘንግ መመታቱን ለማዘከር ነው፡፡

 


 

በዝማሬያቸው

‹‹ሙሻ ሙሾ ስለ ስቅለቱ

አይንፈጉኝ ከዱቄቱ፡፡

ሚሻ ምሾ፣ ሆ ሚሻ ሙሾ

ሳይጋገር መሸ፣

እሜቴ ይውጡ ይውጡ

ይበላዋል አይጡ፣

እሜቴ ይነሱ

ይንበሳበሱ፣

ከቆምንበት

ቁንጫው ፈላበት፣

ስለ አቦ

ያደረ ዳቦ፣

ስለ ስቅለቱ

ዛቅ አድርገው ከዱቄቱ፤››

በማለት ይዘምራሉ፡፡

ሕፃናት ሚሻ ሙሾ ብለው አንድ ቤት ሲጨፍሩ ከቤቱ ዱቄት፣ አዋዜ፣ ቅባኑግ ወይም ጨው ሊሰጣቸው ይችላል፡፡ ይኼንን ሲያገኙ 

‹‹ዕድሜ የማቱሳላን፣

 ጽድቅ የላሊበላን ይስጥልን፤›› ብለው መርቀው ይሄዳሉ፡፡ 

በተጨማሪም ሕፃናት በዚህ ክዋኔ ታላቅ ምርቃት ይሰጣቸዋል፡፡ ሕፃናቱ ለምነው ምንም ነገር ሳይሰጣቸው ከቀረ

‹‹እንደ ሰፌድ ይዘርጋሽ፣ 

እንደ ማጭድ ይቆልምሽ፣ 

ቁመት ያውራ ዶሮ፣ 

መልክ የዝንጀሮ፣ 

ግማት የፋሮ ይስጥሽ፤›› ብለው ተራግመው እንደሚሄዱ አለቃ ታየ ትውፊቱን አስቀምጠዋል፡፡

ሕፃናቱ በልመና ባገኙት ዱቄት ቂጣ ጋግረው ቅዳሜ ምሽት በጋራ ይመገቡታል፡፡ ሊቀ ሥልጣናት አባ ሀብተ ማርያም ወርቅነህ ግን ዳቦውን በትንሣኤ ሳምንት አስጋግረው ጎረቤቶችንና ሽማግሎችን ጋብዘው እንደሚበላ ተናግረዋል፡፡

 ******+++******


 

አርብ ፦ሚሻሚሾ

ሆሆ ሚሻ ሚሾ ሚሻ ሚሾ
አንድ አውራ ዶሮ እግሩን ተሰብሮ
እሜቴ ይነሱ ጉሽጉሻውን ይዳስሱ
ስለ ስቅለቱ ዛቅ አድርገው ከዶቄቱ


እያሉ ህፃናት ተሰብስበው በየቤቱ እየዞሩ የቤቱን ደጃፍ በያዙት ዱላ እየደበደቡ ከላይ ያለውን ግጥም በዜማ ይላሉ። አስቀድመው ግን ዱላ ያዘጋጃሉ ዱላ ሲያዘጋጁም ይልጡትና በልጡ ግማሹን ይሸፍኑትና በእሳት ይለበልቡታል ከዛ ሲወጣ ዝንጉርጉር ይሆናል ነጭና ጥቁር ።በጲላጦስ አደባባይ ጌታችን አጥንቱ እስኪታይ መገረፉን ለማመልከት መሆኑንም ታላላቆቻችን ይናገራሉ.... ሚሻ ሚሾ አንዳንዶች ውሾ ውሾ እያሉ ጌታችንን ማህበራነ አይሁድ መስደባቸውን ለመግለፅ ነው ይላሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ዕለቱ የሐዘን ነው አልቅሱ እዘኑ ለማለት ነውም ይላሉ ምሻሚሾ (ሙሾ-ሐዘን ፣ለቅሶ እንዲል ዱቄቱን ከሰበሰቡ በኃላ ደግሞ ድንጋይ እና ድንጋይ በማጋጨት ጫጫ መሰልቀጫ ሚስቴ ወልዳብኝ ጨውና ዘይት ብላብኝ እያሉ ይዞራሉ ለምን ድንጋይ እንደሚይዙ ግን እስካሁን አልገባኝም በኃላም ከተመረጠ ቤት ይሰበሰቡ እና የሰበሰቡት ዱቄት ተቦክቶ ቂጣ ይጋገራል ከዛ ደግሞ የሰበሰቡት ጨው እና ዘይት ይለወስና ቂጣው ይቀባል ከዛ የሚበላው ተቆርሶ ይሰጠዋል ለሚፆመው ደግሞ ይቀመጥለት እና ከቤተ ክርስቲያን መልስ ትልቁም ትንሹም ከተመረጠው ቤት ቡና ተፈልቶ የሚበላው በልተው ጠጥተው የሚያከፍለውም በጨዋታው መሀል ተገኝቶ ተመራርቀው ይለያያሉ

የአርብ ስቅለት በጎንደር እና አከባቢው እንደዚህ ይከበራል እንደሰማሁት በትግራይ አከባቢ ደሞ ልጃገረዶች ሙሉ ቀኑን በባዶ ሆዳቸው ሆዳቸውን በመቀነት አጥብቀው በማሰር ዥዋዥዌ እያሉ ይውላሉ መንገላታቱን ለማሰብ፤ በዋግም እንደዚሁ፤በጎጃም አገዎችም አጎላ ጎሊ ይባላል።


 በጎጃም አገዎችም አጎላ ጎሊ ይባላል:-


 
 
#EBC ሚሻ ሚሾ/አጎላ ጎሌ በአ እንዴት እንደሚጨፈር እና ምን አይነት ሂደቶችና ስርዓቶች እንዳሉት ያስቃኘናል
 


እጅጋየሁ (ጂጂ) ሽባባው አጎላ ጎሌ


***********************************************

ምንጭ:- https://www.ethiopianreporter.com/article/21944

           :- የጥበብ ወሬዎች