ከደራሲያን ዓምባ

Friday, December 28, 2012

የግጥም ጥግ

አህያ ባረገው


አምነው የጫኑበት
ፈቅደው ያሸከሙት
“አደራ” ነው ያሉት
የስልጣን ሽልጦ፣ የሹመት ዘመራ
ለተጫነው እንጂ፣ ለጫኞች ካልሰራ
ካረገው ተጫኙ - ውኃ፣ ልብስ፣ እንጀራ
ርቦት ከጎረሰው
ጎርሶት ከጠገበው፣
በርዶት ከደረበው
ደርቦት ከሞቀው፣
ጠምቶት ከመጠጠው
መጦት ካሰከረው፣…
ምናለበት እግዜር
አዙሮ ቢጥለው!!
ወይም በጥበቡ፣ ምናል ቢለውጠው!
“እፍ” ያለውን ትንፋሽ፣ መልሶ ቢመርቀው!
ምናል ቢአሳድገው! ምናል ቢመርቀው!
ሰውነቱን ገሮ አህያ ቢአረገው!!
***********************
ምንጭ:-- ( ጌትነት እንየው ‹‹እውቀትን ፍለጋ›› )

No comments:

Post a Comment