ከደራሲያን ዓምባ

Monday, December 16, 2013

ከመጽሃፍት ዓለም

 ሽልንጌን!  ሽልንጌን!  ሽልንጌን!
ፋጤ ወጂን ዴማ
የቀድሞው ስምንተኛ ክፍል የአማርኛ መማሪያ መጽሐፍ
**********************************************

ብርቱኳኗንና መንደሪኗን ይዛ ወደ መንገደኞቹ ባቡር ተጠግታለች:: በጀርባዋ ያዘለችው ሕፃንም “እምቢየው ወደ ቤት እንሂድ፤ እሪ…” እያለ ይነጫነጭባታል::
የእንጀራ ነገር ነውና ይህን የያዘችውን ፍራፍሬ ሳትሸጥ የሕፃን ልጇን ጉሮሮ መዝጋት አትችልም፤ በአንድ እጇ በጀርባዋ ያዘለችውን ሕፃን እያባበለች በሌላ እጇ 
ደግሞ የተሸከመችውን የፍራፍሬ ሰሀን ወደ መንገደኞቹ እያስጠጋች ባቡሩ ከመንቀሳቀሱ በፊት ለመሸጥ በየመስኮቱ ትንጠራራለች:: ይህን ጊዜ ነበር አንዱ 
መንገደኛ እንደ ዘበት በመስኮቱ በኩል እጁን ወደያዘችው ፍራፍሬ ሰዶ አንዱን ያነሳው:: “ሽልንግ” ነው ብላው ሂሳቧን እስኪሰጣት ድረስ በጉጉት
ትጠባበቃለች:: እሱም ሽልንጉን ያስቀመጠበትን ኪሱን መፈተሽ ጀምሯል:: በቀኙ.. በግራው… በፊቱና በኋላዉ ኪሶቹን ይዳብሳል:: የባቡሩ ሞተር መሞቅ ጀምሯል::
መንገደኞች ቦታ ቦታቸውን ይዘው የጉዞውን መጀመር ይጠባበቃሉ:: የባቡሩ ጭስ እየተግተለተለ መውጣት ጀምሯል:: ፋርጎዎቹ መነቃነቅ ጀምረዋል:: ያች
ምስኪን ግን ልቧ ተሸብሯል:: “ኧረ ሽልንጌን” ማለቱን ተያያዘችው:: ደጋግማ ተጣራች:: ፋርጎው ተንቀሳቀሰ ሰውዬው መንደሪኑን በእጁ እንደያዘ 
በሌላኛው እጁ ደግሞ ሽልንጉን ከተቀበረበት ፈልጎ ማውጣቱ ላይ እንዳተኮረ ነው:: አሁን ባቡሩ እየሄደ ነው:: እሷም
ሽልንጌን!...ሽልንጌን!...ሽልንጌን!” እያለች ባቡሩ እየተከተለችው ነው:: ባቡሩ ሄዷል:: የሷም ድምፅ በሩቁ ያስተጋባል::
**************************************************************************************** 
በአንድ ወቅት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአማርኛ የተማሪ መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ባለ አወቃቀርም ባይሆን በተመሳሳይ መልኩ በወጉ ተጽፎ
የቀረበ ታሪክ ነበር:: ይህ አጭር ልብ ወለድ ታሪክ በአብዛኛው የዘመኑ ተማሪ ሕሊና ውስጥ ታትሞ ለረጅም ዘመን መቆየት የሚያስችለው ኪነ ጥበባዊ
አቅም ነበረው:: ይህ ታሪክ ከኪነ ጥበባዊ ተፈጥሮው ባሻገር የዛን ዘመኑን የባቡር እንቅስቃሴንና የድሬዳዋ ከተማን ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን ምስል ከሳች በሆነ
መልኩ አሳይቶ ያለፈ ነበር::
ደራሲው ማን ይሆን?
ማግኝት ይቻል ይሆን ?
ያላችሁ ተባበሩን ?
በትውስታ እንቆዝምበት!!!

1 comment:

  1. ሚስተር ቤንጃሚን የኢሜል ዝርዝሮችን እነሆ ፣ Lfdsloans@outlook.com ፡፡ / ወይም ደግሞ ንግዴን ለመጀመር በ 90,000.00 ዩሮ ብድር የረዳኝ WhatsApp + 1-989-394-3740 እና እኔ በጣም አመስጋኝ ነኝ ፣ እዚህ አንድ ነጠላ እናት ነገሮች እንዳላደረጉ መንገድ ለመፍጠር እየሞከርኩ ነው ፡፡ ከእኔ ጋር ቀላል ይሁኑ ግን ንግዴ እየጠነከረ ሲመጣ እና እያሰፋ ሲሄድ እያየሁ በሚስተር ሚስተር እርዳታ ፊቴ ላይ ፈገግታ አሳየኝ ፡፡ የገንዘብ ድጋፍን መፈለግ ወይም በዚያ ንግድ ውስጥ መከራን ማለፍ ወይም የመነሻ የንግድ ሥራ ፕሮጀክት መጀመር መፈለግ ይህንን ማየት እና ከችግራቸው ለመውጣት ተስፋ ሊኖረው ይችላል ... እናመሰግናለን ፡፡

    ReplyDelete