ከደራሲያን ዓምባ

Monday, November 16, 2020

ባለ አጉረምራሚ ድምጹ "ጎልደን ቮይስ" ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ

 

ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ

ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴን ብዙዎች እንደሚያውቁት አስባለሁ። በተለይ በጉልምስና ዕድሜና ከዛም ከፍ ባለ የዕድሜ ክልል የሚገኘው ኢትዮጵያዊ አለምነህ ዋሴን ያውቀዋል። በደርግ ዘመን በኢትዮጵያ ሬድዮ ውስጥ ሲሰራ ለየት በሚለው ጆሮ ገብ ድምጹና ልዩ በሆነው የዜና አቀራረቡ ተወዳጅ እንደነበር ራሴን አንድ ብዬ በማስረጃ ምስክርነት እጠራለሁ።

ዜና-ፋይል! የሚለው የዜና አቀራረብ ፎርማት ሲታወስ አለምነህ ዋሴ፤ ዳሪዎስ ሞዲ፤ ነጋሽ መሐመድ፤ ንግስት ሰልፉን ... የማያስታውስ ካለ እሱ በዛ ወቅት ያለጥርጥር ከኢትዮጵያ ውጭ ነበር። የዛሬውን አያድርገውና በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት ብቸኛዋ የዜናና የመረጃ  ምንጫችን ስለነበረች እነ አለምነህን አለማወቅ አይቻልም።

በተለይ አለምነህ ዋሴ ደግሞ በአሜሪካና ኢራቅ ጦርነት ወቅት የሚያቀርበው ዘገባ እንዴት በጉጉት ይጠበቅ እንደነበር ሳስታውስ፤ ዜና ድሮ ቀረ! ለማለት ይዳዳኛል።

አለምነህ ዋሴን ከምናስታውስባቸው ስራዎቹ ዋናው የአሜሪካና ኢራቅ ጦርነት ዘገባው ነው።

በዛ ወቅት በማለዳው የኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት ዜና አለምነህ፤ 

 

”ባግዳድ ጸጥ ረጭ ብላ አድራለች፤ ምድሯን የተቆለመመ ብረት፤
የግንብ ፍርስራሽ፤ አቧራ ... ሞልቶታል” 

 

እያለ በዓይነ ልቦናችን ወደ ባግዳድ ተጉዘን አዳሯን እንድንመለከት የሚያደርግበትን አቀራረቡን ዛሬም ድረስ በከፊልም ቢሆን አስታውሰዋለሁ። ስእላዊ ዜናውን ያቀርብልን የነበረው ምናልባት በምስል ያገኘውን የባግዳድን የማለዳ ገጽታ ወደ ቃላት ተርጉሞ፤ አልያም ገጽታውን የዘገበ ዜና ወደ አማርኛ መልሶ ይመስለኛል። ያም ሆነ ይህ አለምነህ በአሜሪካና ኢራቅ ጦርነት የማይረሳ አሻራውን በማሳረፉ ሁላችንም የምንስማማ ይመለኛል።

 

 “እጅ መስጠት የለም አሉ ሳዳም ሁሴን” 

 

የሚለው ድምጹ ዛሬም ድረስ ይሰማኛል።

እንዳሁኑ መረጃ ከአንዱ የዓለም ጫፍ ወደ ሌላው የዓለም ጫፍ በብርሃን ፍጥነት በማይደርስበት በዛን ወቅት አለምነህ ዋሴ የአሜሪካና የኢራቅን ጦርነት እግር በግር ተከታትሎ የሚዘግብልን ከዓለም አቀፍ የዜና ዲስፓች ላይና ከእንግሊዘኛ መጽሔቶች ላይ እንደነበር ሲናገር የሰማሁ ይመስለኛል። በግዜው እሱም ከኢ.ዜ.አ. የዜና ዲስፓች ሌላ አማራጭ አልነበረውም። እኛም እሱን ከመስማት በስተቀር ሌላ አማራጭ አልነበረንም።

 

ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ 

 
 
 
https://www.youtube.com/watch?v=3dVNaqsLl4A

https://Interview with Journalist Alemneh Wasse on Yezinegnochu Chewata program Zami Radio.youtube.com/watch?v=VHSvzaAEL_k 


 


ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ


 
 

 

 

No comments:

Post a Comment