ከደራሲያን ዓምባ

Wednesday, November 25, 2020

ለሰው ልጆች ሰላም

ለሰው ልጆች ሰላም  

ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ

 *************************


 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
ለሰው ልጆች ፍቅር ለሰው ልጆች ሰላም
ለሰው ልጆች ፍቅር ለሰው ልጆች ሰላም
ለሰው ልጆች በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ሰላም ይሁን ምድሩ ሁሉ

ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ
ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ

ከባሕር ከየብሱ ከሰፊው ውቅያኖስ
በሚመጣው አየር በሚነፍሰው ንፋስ
ያለን መልካም ምኞት ያለን ቀና መንፈስ
የሰላም ጥሪያችን መልዕክታችን ይድረስ
የተበከለ አየር ጠፍቶ ከላያቸው
የዱር አራዊቶች አእዋፍ በጎጇቸው
ሁሉም በያሉበት በየበኩላቸው
የሰላሙ ፋና ይድመቅ ይብራላቸው

በዓለም በዓለም
ይስፈንልን ሰላም
በዓለም በዓለም
ይስፈንልን ሰላም
ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ
ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ


 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
ህጻናት እንዲያድጉ በንጹህ አይምሮ
ነጻ ህሊናቸው ጎልብቶና ዳብሮ
ወጣት ሽማግሌ የሰው ዘሮች ሁሉ
ሰላም ለዓለማችን ይላሉ በሙሉ
ዘንባባ ዘንጥፈን እርግቦችን ለቀን
ዘር ቀለም ሳንለይ ጥላቻን አርቀን
ለሰው ልጆች ደስታ ለሰው ልጆች ፍቅር
ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ ለሰላም እንዘምር

በዓለም በዓለም
ይስፈንልን ሰላም
በዓለም በዓለም
ይስፈንልን ሰላም

ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ
ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ
ሰላም
ሰላም
ሰላም
በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ለሰው ዘር በሙሉ
 

‹‹ለሰው ልጆች ሰላም. . .››  22 November 2020

 ***********

ከ1980ዎቹ መባቻ ጀምሮ በሬዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ይሰማ፣ ይደመጥ የነበረ አሁንም ደግሞ ሞገድ አሳብሮ የሚሰማ የሚደመጥ አንድ ዜማ/ዘፈን አለ፡፡

‹‹ለሰው ልጆች ፍቅር ለሰው ልጆች ሰላም፣

ለሰው ልጆች በዓለም ዙሪያ ሁሉ

 ሰላም ይሁን ምድሩ ሁሉ፡፡››

ታዋቂውና አንጋፋው ድምፃዊ መሐመድ አህመድ ያቀነቀነው ሌሎች ድምፃውያንም በኅብረ ዝማሬ ዓምና ያቀረቡት የሰላም ጥሪ፣ የሰላም ደወል ነው፡፡


 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

በየዐረፍተ ዘመኑ ስለኢትዮጵያ ሰላም ያልተዘመረበት ያልተገጠመበት፣ ያልተተወነበት ጊዜ የለም፡፡ ሁሉም በየቤተ እምነቱ፣ በየደጀ ሰላሙ ስለሰላም ጸልየዋል፣ ስለሰላም ዘምረዋል፣ ስለ ሰላም አልቅሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ በየዐረፍተ ዘመኑ የሰላም ድምፅ እየራቀ፣ ሁከት እየሰፈነና፣ ጦር ንቅነቃ፣ ዘገር ውዝወዛ መንሰራፋቱ ሰውን ለጥፋት፣ ለስደት፣ ለጉዳት መዳረጉ አልቀረም፡፡

ሰላምና ጽንሰ ሐሳቡ

በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በተዘጋጀው ‹‹መዝገበ ቃላት ሐዲስ›› የሰላምን ፍች ከሌሎች የምሥራቅ ሴማዊ ቋንቋ ቤተሰብ ስያሜ ጋር አያይዘው አቅርበውታል፡፡ ሰላም በሱርስት (የሶርያ ቋንቋ) ሽላም፣ በዕብራይስጥ (የእስራኤል ቋንቋ) ሻሎም፣ በዓረብ ሰላም እንደሚባል ትርጉሙም ፍፁም ጤናን፣ ዕረፍትን፣ ዕርቅን፣ ፍቅርን አንድነትን፣ ደኅንነትን፣ ተድላ ደስታን፣ ሰላምታን ያቀፈ ጽንሰ ሐሳብ ነው ይሉታል፡፡ ሰላም ሰው ሲገናኝ፣ ሲለያይ የሚለው፣ የሚናገረው ወይም የሚጥፈው የቡራኬ የምርቃት ቃል ነው ሲሉም ያክሉበታል፡፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ‹‹የሰላም ግንባታ ማሠልጠኛ›› በተሰኘው ጥናታዊ መድበሉ ስለ ሰላም ምንነት እንደሚከተለው አብራርቷል፡፡

‹‹ሰላም›› የሚለው የአማርኛ ቃል የተሸከመው ጽንሰ ሐሳብ ከጦርነትና ከአመፅ ነፃ መሆን ከሚለው የአንዳንድ መዛግብት ቃላት ውሱን ድንጋጌ የሰፋ ትርጉም ይዟል፡፡ ‹‹ሰላም›› ለሰው ልጆች ከእግዚአብሔር የተሰጠ ስጦታና ከመለኮታዊ ዕድቅ ጋር የሚጣጣም ሰብዓዊ ዕቅድ ከመሆኑ በፊት በዋናነት የእግዚአብሔር የራሱ ዓይነተኛ ባህሪ  ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ‹‹እግዚአብሔር ሰላም ነው›› (መጽሐፈ መሳፍንት 6፡24) በማለት ማረጋገጫውን ሰጥቷል፡፡

‹‹በቅዱሳት መጻሕፍት ሰላም የሚለው መሠረታዊ ቃል የሚያመለክተው በሰዎች ሕይወት ውስጥ ተሟልቶ መገኘት የሚገባውን ደኅንነት፣ ምሉዕነት፣ ፍፁምነትና ዋስትናን በመሆኑ ቃሉ የያዘው ፍቺ ላቅ ያለ ሐሳብን ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ ሰላም ማለት ሰዎች በግል ኑሯቸውም ሆነ በማኅበራዊ ግንኙነታቸው ወቅት ሊኖራቸው የሚገባ ሁለንተናዊና ምሉዕ የሆነ የሕይወት መገለጫ ነው ማለት ይቻላል፡፡

‹‹ሰላም›› (Sala’am) የሚለው የዓረብኛው ቃልም እንዲሁ ቀደም ሲል ከተጠቀሱት ጽንሰ ሐሳቦች ጋር ተመሳሳይ ትርጉም ከመያዙ በተጨማሪ በምድራዊም ሆነ በመንፈሳዊ ዓለም ከአደጋ ነፃ የሆነ የጤናማ ሕይወት ማረጋገጫ የሚል ከፍ ያለ ትርጉም ተሸክሟል፡፡

በግዕዝ ቋንቋም ሰላም ቀደም ሲል የተጠቀሱት ትርጉሞች እንደ ተጠበቁ ሆነው ማክበርን፣ ደስታን፣ ዋጋን የሚመለከት ትርጉም እንዳለው የሚያብራራው መድበሉ፣ ይህንን መሰል ሰላም ማግኘት የሚቻለው ራስን ከፈጣሪ ሐሳብ ጋር በማስማማት፣ ከተፈጥሮ ጋር በመታረቅና ከማኅበረሰብ አንፃርም ፍትሕና ማኅበራዊ መረጋጋት ባሰፈነ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ መኖር ሲቻል መሆኑን ያስገነዝባል፡፡

ሰላም ሰዎች ከራሳቸው ጋርና እርስ በርስ፣ ከፈጣሪና ከተፈጥሮ ሥርዓት ጋርም እንዲሁ ጤናማ ግንኙነት በመፍጠር በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ ሥርዓት፣ በማኅበራዊና በመንፈሳዊ ዘርፎች ውስጥ ዋስትና የሚሰጥና የሰከነ ሕይወት የሚመሩበት እንደሆነም ያሰምርበታል፡፡ ሰላም ለሰዎች ሁለንተናዊ ሕይወት ዋስትና በመስጠት ምቹ ሁኔታን ስለሚፈጥር የጽንሰ ሐሳቡ ትርጉም ሲተነተን ሰፋ ተደርጎ እንጂ በቁንፅል ሊሆን እንደማይገባም እንዲሁ፡፡

ሰላም የባህል አንዱ ክፍል መሆኑን፣ ባህልም የአንድ ሕዝብ ሁለንተናዊ መገለጫ፣ ማለትም ኅብረተሰቡ የተፈጠረበትን ማኅበረሰብ ቁሳዊና መንፈሳዊ ሕይወት በተገቢ ሁኔታ የማንፀባረቅ አቅሙ ከፍ ያለ እንደሆነም ያብራራል፡፡

የማኅበረሰቡ ሐዘን፣ ደስታ ችግሩና ብልፅግናው የሚገልጸው በባህሉ ሲሆን፣ የዜጎች ሁለንተናዊ የግልና የማኅበራዊ ሕይወት አመራር ሥልት የሚወሰነውም በባህል አማካይነት ነው፡፡ አንድን ማኅበረሰብ ከሌላው ልዩ የሚያደርገው መታወቂያ በዋነኛነት ባህሉ ነው የሚባለውም ስለዚሁ ምክንያት መሆኑን ጥናቱ ገልጾ በማሳያነት እንግዳ ተቀባይነትን፣ ተካፍሎ በጋራ መብላትን፣ ተከባብሮና ተፈቃቅሮ መኖሩ፣ ዕድር ዕቁቡ፣ ሠርግ ሐዘኑ፣ አለባበስ አመጋገቡ ወዘተ. ስለባህል ብዙ የሚነገረውን ያህል፣ ስለሰላም ባህል እጅግም ሲነገር አይደመጥም ሲል አሳሳቢ ገጽታውን ይጠቁማል፡፡


የሰላም ባህል፣ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች፣ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በጋራ በሚኖሩባት ኢትዮጵያ በሰላም ተከባብረው ለዘመናት እንዲኖሩ ያስቻላቸው የአኗኗር ዘይቤ መሆኑን፣ የሰላምን ቀጣይነት ከሚያረጋግጡትና ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው የሰላማዊነት መገለጫ ባህላዊ እሴቶች መካከል ቤተሰብ ተኮር የሰላም ባህል አንዱና ቀዳሚው መሆኑንም ይገልጻል፡፡

በኢትዮጵያ ለረዥም ዘመናት ጠንካራ የሰላም ባህል እንዲኖር ቤተሰብ ተኮርነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን እንደሚከተለው ገልጾታል፡፡

‹‹የሰላም ባህላችንን ውበት ለመግለጽ የማኅበረሰባችን መሠረት የሆነውን የቤተሰብ አስተዋጽኦ ማውሳት እጅግ ጠቃሚ ይሆናል፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን ብዙውን ጊዜ በፍቅርና በመከባበር በጋራ ሠርተን የምንኖረው፣ አደጋን የምንከላከለው፣ ሰላማዊ ሕይወት ለመምራት የምንለማመደውና መተባበርን የምንለማመደው በቤተሰብ መካከል በመኖር ነው፡፡ የአመለካከት ልዩነቶችን የምንፈታውና ለቤተሰቡ የጋራ ደኅንነትና ዕድገት ጠቃሚ መንገዶችን የመቀየስ ልምድ የምንማርበት ትልቁ ትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ነው ቢባል ከእውነት አያርቀንም፡፡››

እንደ ጥናታዊው መድበል አገላለጽ፣ በየዘመናቱ ለሕዝቡ ሰላምና የጋራ ዕድገት ቅድሚያ እየሰጡ ያታገሉና የታገሉ ጀግኖችም አገራቸውን እንደ ቤተሰብ በመቁጠር ታላላቅ የሚሰኙ አገራዊ ቅርሶች ሊያቆዩ የቻሉት ቤተሰብ ተኮር መሠረት ላይ ታንፀው በማደጋቸው ነው፡፡

በአንፃሩም በጋራ ሠርቶ በጋራ ማደግ፣ ከራስ ጥቅም ይልቅ አገርንና ሕዝብን ማስቀደም የሚሳናቸው ግለሰቦች እየተነሱ መነጋገሪያ ለመሆን የቻሉበት ሲመረመር ምክንያቱ ምናልባትም በቤተሰብ ተኮር እሴት ላይ የማደጉን አጋጣሚ ስላልተመቻቸላቸው ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አይከብድም፡፡

የብዙ ኢትዮጵያውያን ዕድገት፣ ኑሮ፣ ደስታ፣ ሐዘን፣ ወዘተ. ከቤተሰባዊ አብሮነት ጋር በእጅጉ የተሳሰረ በመሆኑ፣ በቤተሰቡ መካከል ሰላማዊ ግንኙነት እንዲቀጥል እያንዳንዱ ዜጋ ብርቱ ጥረት ማድረግ አለበት፡፡ በማኅበረሰቡ ውስጥ ሥር ሰዶ የሚገኘው የቆየው የሰላም ወዳድነት ምንጭም ዜጎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ከቤተሰቦቻቸው ከተማሯቸው ሰው አክባሪነትና በጋራ ሠርቶ የማደግ መሠረት ላይ የታነፀ እንደሆነ መረዳት አያዳግትም የሚለው ጥናቱ፣ በመሆኑም ዘላቂ ሰላም በማስፈን ቁሳዊ፣ መንፈሳዊ፣ ሥነ ልቦናዊም ሆነ ማኅበራዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ቤተሰባዊ ውርስ የሚኖረው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ያሰምርበታል፡፡

 **************************************************

ምንጭ:- https://www.ethiopianreporter.com/article/20539


 

 

 

 

No comments:

Post a Comment