ከደራሲያን ዓምባ

Thursday, September 29, 2022

"የማሽላው አባት!"__ ተመራማሪ እና የዓለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኢጀታ

 

ዓለም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሰሩት ሥራ በአለም መድረክ ስማቸውንና የሀገራቸውን ስም ያስጠሩ ፀኃፊ፣ አርታኢ፣ መምህር፣ አማካሪ እና ተመራማሪ የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታን ከረጅሙ የሂወት ጉዞአቸው በጥቂቱ ይዘንላቹ ቀርበናል፡፡

ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ከአዲስ አበባ ስልሳ ሁለት ኪሎሜትር በስተ ምእራብ እርቀት ላይ በምትገኘው ኦሎንኮሜ በ1950 እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር ተወለዱ፡፡ የቄስ ትምህርታቸውን በአካባቢያቸው ሲከታተሉ ቆይተው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት በአካባቢያቸው ስላልነበረ 20 ኪሎሜትር በግራቸው ተጉዘው ተከታትለዋል፡፡



የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጅታ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጅማ የግብርና ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ የተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በእፅዋት ሳይንስ ከአለማያ ኮሌጅ በ1973 ዓ.ም ወስደዋል፡፡ እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ1976 በእፅዋት ሳይንስ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በ1978 በእጽዋት ማዳቀል እና ዘረመል ኢንጂነሪንግ አሜሪካ ከሚገኘው ፔድሩ ዩኚቨርስቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡

ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጅታ ከሁለት መቶ በላይ የጥናት ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን አራት መፅሐፎችን የአርትዎት ስራ ሰርተዋል፡፡

ላለፉት 28 አመታት በአሜሪካ በሚገኘው ፔድሩ ዩኚቨርስቲ ያገለገሉት የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ዩኒቨርስቲው አሉኝ ከሚላቸው ተመራማሪዎችም አንዱ ናቸው፡፡ ዶክትሬታቸውን ከተመረቁ በሆላ ወደ ሱዳን በመሄድ ማሽላ ላይ ምርምራቸውን ቀጥለዋል፡፡ በምርምራቸውም ድርቅን መቋቋም የሚችል የማሽላ ዘርያ ለአለም ማህበረሰብ ማበርከት ችለዋል፡፡ በ150 እጥፍ ምርታማነትን የሚጨምር የማሽላ ዝርያን ለአለም አበርክተዋል፡፡ ድርቅን መቋቋም የሚችል የማሽላ ዝርያ ላይ ባስገኙት ውጤት ከአምስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ አፍሪካዊያን የምግብ ዋስትንን ማረጋገጥ ችለዋል፡፡



ጥናታቸው በዚህ ሳያበቃ በአፍሪካ ምርታማነትን በ40 በመቶ የሚቀንሰው እስትራጋ የሚባለውን አረም መቋቋም የሚችል የተሸሻለ የማሽላ ዝርያን ኢትዮጲን ጨምሮ ለ12 አፍሪካ ሃገሮች ማቅረብ ችለዋል፡፡
ለእነዚህ እና መሰል የምርምር ስራዎቻቸው ከ17 በላይ አለም አቀፍዊ ፣ ሀጉራዊ እና ሀገራዊ ሽልማቶችን አግኝተዋል፡፡ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2009 ወርልድ ፉድ ኖብል ፕራይዚ የተሸለሙ ሁለተኛው አፍሪካዊ ለመሆን በቅተዋል፡፡ በአፍሪካ ናሽናሊቲ ሳይንስ ሂሮ ሽልማት ከተሸለሙ አፍሪካዊ ሰባት ተመራማሪዎችም አንዱ መሆን ችለዋል፡፡

ከሰባ በላይ አለም አቀፍ እና ሀገራዊ ተቋሞች በተለያዩ የሀላፊነት ደረጃዎች ላይ የሰሩት የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የአለም ህዝብ ቁጥር በጨመረ ቁጥር የምግብ ፍላጎት እየጨመረ ይመጣል ይህን ለመቋቋም ሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና የምርምር ፈጠራ ውጤቶች በመጨመር ይሄንን መቋቋም የግድ የሚል ነው ይላሉ፡፡ ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2011 በፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ የአለም አቀፍ የምግብ እና ግብርና ልማት ቦርድ ውስጥ እንዲሁም ከ2014 ጀምሮ በዩናይትድ ኔሽን ሴክሬተሪ ጄነራል ባኒኪሞን የዩዔን የሳይንስ አማካሪ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡


SOURCE:- Technology and Innovation Institute, Ethiopia

No comments:

Post a Comment