ከደራሲያን ዓምባ

Wednesday, October 12, 2022

አንጋፋው የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔ ሲታወሱ

 


1927 ዓ.ም - 2015 ዓ.ም 

በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ታሪክ በዋናነት የሚነሱት ጋዜጠኛና ደራሲ ፍቅሩ ኪዳኔ የተወለዱት በ1927 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ነው።

አባታቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ የነበሩ ሲሆን፣ የክለቡን ተጫዋቾች ከትምህርት ቤት ወደ ስታዲየም ይዞ በመሄድ ይታወሳሉ፡፡

በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ ከአባታቸው ጋር የመሆን ዕድል የነበራቸው አቶ ፍቅሩ በኋላ የስፖርት አስተማሪ ሆነዋል።

በኢትዮጵያ ሬዲዮና የተለያዩ የአገር ውስጥ የሕትመት ውጤቶች ስለ አገር ውስጥ ስፖርት መዘገብ የጀመሩት አቶ ፍቅሩ በ1943 ዓ.ም በሱዳን እና ኢትዮጵያ መካከል የተደረገውን ጨዋታ በቀጥታ በሬዲዮ ማስተላለፍ የቻሉ የመጀመሪያው የስፖርት ጋዜጠኛ ናቸው።

አቶ ፍቅሩ የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር በ1961 ዓ.ም ሲመሰረት የመጀመሪያው ፕሬዝደንት የነበሩ ሲሆን በብስክሌት ፌዴሬሽን፣ቴኒስ ፌዴሬሽን እና በኢትዮጵያ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀሐፊነት፣ በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን የሕዝብ ግንኙነት በመሆን አገራቸውን አገልግለዋል፡፡

በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውስጥም በአመራርነት ፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የቀድሞ ፕሬዝደንት የነበሩት የኢሳ ሃያቱ አማካሪ ጭምር የነበሩ ፡፡

ከ1969 ዓ.ም ጀምሮ ኑሯቸውን በፈረንሳይ መዲና ፓሪስ ያደረጉት አቶ ፍቅሩ በአገሪቷ ለሚገኘው ዕለታዊ የስፖርት ጋዜጣ ለኪፕ እና ሳምንታዊ የእግር ኳስ መጽሔት ፉትቦል ፍራንስ፣ ዶቼቬሌ (የጀርመን ድምፅ) እና ሌሎች የአለም አቀፍ ታዋቂ መገናኛ ብዙሃን መስራት ከመቻላቸው በተጨማሪ “የፒያሳ ልጅ” እና “የስፖርት ጨዋነት ምንጮች” የተሰኙ መጻሕፍት መጻፍ ችለዋል፡፡

ጋዜጠኛና ደራሲ ፍቅሩ ኪዳኔ አንድ ልጅ ያላቸው ሲሆን ሁለት የልጅ ልጆችንም አይተዋል።

ደራሲ -  ፍቅሩ ኪዳኔ

አከፋፋይ - ዓይናለም የመጻሕፍት መደብር

ዋጋ - 70 ብር

የታተመበት ዓመት - 2001 ዓም

የፒያሳ ልጅ በአስራ ስድስት ምእራፋት ተከፋፍሎ፤ 456 ገፆች ሲኖሩት፤ 
ከሃምሳ በላይ በሚሆኑት ገፆቹ “እንዴት አይናገር ይናገራል ፎቶ…” እንዲሉ፤ 
ማራኪና ታሪካዊ የሆኑ የፎቶግራፍ ማስረጃዎች ያካተተ ሲሆን የህትመት ዘመኑም 2009 ዓ.ም  

አንጋፋው የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔ ሲታወሱ


በኢትዮጵያ የተለያዩ ስፖርቶች ውስጥ አሻራቸውን ካሳረፉ ሰዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ።

በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያውን የእግር ኳስ ግጥሚያ በሬዲዮ ከማስተላለፍ አንስቶ፣ በሬዲዮና በጋዜጣ ላይ ስፖርትን የሚመለከቱ ዘገባዎች ቦታ እንዲያገኙ አድርገዋል።

በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማት ውስጥ ጉልህ ሚና ካላቸው ጥቂት ኢትዮጵያውያን መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በ87 ዓመታቸው ያረፉት አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ እንዴት ይታወሳሉ?

መስመር

በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኝነት ሙያ የመጀመሪያው የእግር ኳስ ግጥሚያ በሬዲዮ ከማሰራጨት እስከ ፀሐፊ እና የስፖርት ሕትመቶች ዋና አርታዒነት ደርሰዋል።

በስፖርት እውቀታቸው ዓለም አቀፍ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ሴክሬታሪያት ፀሐፊ ሆነው አገልግለዋል። በዘረፉ ለስመዘገቡት አስተዋጽኦ በዓለም አቀፉ የስፖርት ፕሬስ ማኅበር የሕይወት ዘመን ስኬት ሽልማትን ተቀብለዋል።

ጥቅምት 01/2015 ዓ.ም. ፈረንሳይ ውስጥ በ87 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን አንጋፋውን የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔን ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛው ገነነ መኩሪያ “የሕይወት ዘመናቸውን በሙሉ ለኢትዮጵያ ስፖርት ያዋሉ” ሲል ይገልጻቸዋል።

የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠ ታዋቂው ፍቅሩ ኪዳኔ ከቀድሞው የ IOC ፕሬዝዳንት ሁዋን አንቶኒዮ ሳምራንች ጋር


ፍቅሩ ኪዳኔከኔልሰን ማንዴላ ጋር

የመጀመሪያው የእግር ኳስ ግጥሚያ በሬዲዮ

አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ እአአ 2016 ላይ ለሲቢሴስ አማርኛ ሲናገሩ፤ በኢትዮጵያ የሕትመት ውጤቶች እና የሬዲዮ ስርጭት ውስጥ የስፖርት ፕሮግራሞች እንዲከፈቱ ጥረት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።

አቶ ፍቅሩ እርሳቸው በጀመሩት የመጀመሪያው የሬዲዮ ፕሮግራም የኢትዮጵያ እና የሱዳን ብሔራዊ ቡድኖችን የእግር ኳስ ግጥሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ ማሰተላለፋቸውን ይገልጻሉ።

አቶ ፍቅሩ ይህን ጨዋታ እንዴት በሬዲዮ እንዲያስተላለፉ የተደረገው በድንገትና ሳያስቡት ነበር። ይህም ጨዋታውን ለሕዝብ ጆሮ እንደሚያደርሱ ሳይነገራቸው እና ምንም አይነት ዝግጅት ሳያደርጉ ነበር የመጀመሪያውን የቀጥታ ሥርጭት ያስተላለፉት።

አቶ ፍቅሩ ይህን ጨዋታ እንዴት በሬዲዮ እንዲያስተላለፉ የተደረገው በድንገትና ሳያስቡት ነበር። ይህም ጨዋታውን ለሕዝብ ጆሮ እንደሚያደርሱ ሳይነገራቸው እና ምንም አይነት ዝግጅት ሳያደርጉ ነበር የመጀመሪያውን የቀጥታ ስርጭት ያስተላለፉት።

ሱዳኖች የእግር ኳስ ጨዋታውን ከአዲስ አበባ በቀጥታ በሬዲዮ እንደሚያስተላልፉ የተረዱት አቶ ይደነቃቸው ተስማ፣ እኛስ ለምን አናስተላልፍም? በማለት ሐሳቡን በድንገት እንዳመጡት ጋዜጠኛ ገነነ ይናገራል።

ከዚያም ከኢትዮጵያ ሬዲዮ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር የቀጥታ ሥርጭቱ በመፈቀዱ ጨዋታው ከመጀመሩ ከደቂቃዎች በፊት አቶ ፍቅሩ እንደሚፈለጉ በድምጽ ማጉያ ተጠርተው ነበር በድንገት ተጠርተው የቀጥታ ሥርጭት ማይክሮፎን የቸበጡት ይላል ገነነ።

አቶ ፍቅሩም “ጨዋታው ሊጀመር 10 ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩት ትፈለጋለህ ተብዬ ተጠርቼ ስሄድ፣ አቶ ይድነቃቸው አንተ እኮ ነው የምትፈለገው ብሎ የተጫዋቾችን አሰላለፍ ሰጥቶ ጨዋታውን እንዳስተላልፍ ነገረኝ” ሲሉ አስታውሰዋል።

“ጨዋታው ሊጀመር 10 ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩት ትፈለጋለህ ተብዬ ተጠርቼ ስሄድ፣ አቶ ይድነቃቸው አንተ እኮ ነው የምትፈለገው ብሎ የተጫዋቾችን አሰላለፍ ሰጥቶ ጨዋታውን እንዳስተላልፍ ነገረኝ።”

ከዚያ በኋላ በኢትዮጵያ የስፖርት ውድድር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ስታዲዮም (በ1948 ዓ.ም.) የእግር ኳስ ጨዋታ በሬዲያ በቀጥታ በሬዲዮ በማስተላከፍ አቶ ፍቅሩ ቀዳሚው ሆኑ።

በሕትመት ውጤቶች ላይም ቢሆን ስፖርታዊ ጉዳዮችን መዘገብ የተጀመሩት በአቶ ፍቅሩ ጥረት ነበር። ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ ለቢቢሲ ሲናገር፤ “በጋዜጦች ላይም ስፖርት የሚባል አይታወቅም ነበር። ከ1950 በኋላ ፍቅሩ ነበር መጻፍ የጀመረው።”

ጫማ ለአበበ ቢቂላ

ገነነ እንደሚለው በባዶ እግሩ የኢሊምፒክ ማራቶንን በማሸነፍ የሚታወቀው የዓለማችን ታላቁ የማራቶን ሯጭ አበበ ቢቂላ በጫማ እንዲሮጥ ያደረጉት አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ ናቸው።

“ፍቅሩ ከአንድ ጫማ አምራች ድርጅት ጋር ተነጋግሮ ለአበበ በነጻ የመሮጫ ጫማ እንዲሰራለት አስደርጓል። ጫማ አምራቹም በአበበ ስም ታዋቂነትን ለማግኘት ችሏል።”

በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ ሲሰሩ የቆዩት አቶ ፍቅሩ፣ ወታደራዊው መንግሥት ወደ ሥልጣን በመጣበት ጊዜ እንደወጡ ቀርተው ለበርካታ ዘመናት በተለያዩ አገራት ውስጥ ኖረዋል።

ነገር ግን ባሉበት ሆነው በኢትዮጵያ የተለያዩ ስፖርቶች እንዲጎለብቱ የሚችሉትን አስተዋጽኦ ሲያበረክቱ ቆይተው፤ አብዛኛውን እድሜያቸውን በቆዩባቸው የውጭ አገራት ውስጥ ሆነው እንኳን ለኢትዮጵያ ስፖርት ሲሰሩ እንቆዩ ገነነ ገልጿል።

አቶ ፍቅሩ በኢትዮጵያ የተለያዩ ስፖርቶች ውስጥ ፍቅሩ ያልገቡበት ዘርፍ የለም የሚለው ገነነ፣ አሁን ትኩረትን እየሳበ ያለው የሴቶች እግር ኳስ እንዲጎለበት የአቶ ፍቅሩ ሚና ጉል እንደነበር ይጠቅሳል።  

ፍቅሩ ከእግር ኳስ ባሻገር በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ውስጥ ኢትዮጵያ ውክልና እንዲኖራት በግሉ የቻለውን ሁሉ ሲያደርግ እንደቆየ የሚናገረው ጋዜጠኛ ገነነ፤ ብዙም አቅም የሌላቸው የስፖርት ፌዴሬሽኖችን በመወከል በእራሱ ወጪ በዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ላይ ይሳተፍ ነበር።

እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ የነበረውን የዘር መድልዎ (አፓርታይድ) ሥርዓት በመቃወም አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮች እንድትታገድ ከአቶ ይድነቃቸው ተሰማ ጋር ከፍተኛ ጥረት ከማድረግ ባሻገር፤ በዓለም አቀፍ ሕትመቶች ላይ ፀረ አፓርታይ የቅስቀሳ ጽሁፎችንም ያቀርብ እንደነበር ገነነ አስታወሷል።

የዓለም ዋንጫን በፕሮጀክተር

አቶ ፍቅሩ ስፖርት በመገናኛ ብዙኃን ላይ ቦታ እንዲያገኝ ከመጣራቸው ባሻገር፣ ቴሌቪዥን ባልተስፋፋበት በዚያ ዘመን ከአዲስ አበባ ውጪ ያለው ስፖርት አፍቃሪ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን እንዲመለከትም አስችለዋል።

ለዚህም እአአ 1958 በስዊዲን አገር ተካሂዶ የፔሌ ትውልድን የያዘው የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ዋንጫ የወሰደችበትን ግጥሚያ አቶ ፍቅሩ በክፍለ አገር ከተሞች እየተጓዙ በፕሮጀክተር ጨዋታውን ያሳዩ እንደነበረ ጋዜጠኛ ገነነ ይናገራል።  

“እኛ ፔሌ፣ ጋሪንቻ የሚባሉትን በስም እንኳ አናውቃቸውም ነበር። እሱ በየክፍለ አገሩ ዞሮ ካሳየ በኋላ ነው ተጫዋቾቹ ኢትዮጵያ ውስጥ የታወቁት።”

አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ በስፖርት ጋዜጠኝነት ሙያ ከማገልገላቸው በተጨማሪ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ፣ የማስታወቂያ ባለሙያ ሆነውም ሠርተዋል።

በተጨማሪም በመንግሥታቱ ድርጅት በኩል ኢትዮጵያ ወደ ኮንጎ ጦሯን ባሰማራችበት ወቅት ጦሩን የሚመሩት የኢትዮጵያ ጄኔራሎች ፈረንሳይኛ የሚናገር ወጣት በመፈለጋቸው፣ ፍቅሩ የመቶ አለቃ ማዕረግ ይዘው ወደ ኮንጎ መዝመተውም ነበር።

ይህ አጋጣሚ ነበር አቶ ፍቅሩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ የሥራ ዕድል በር ከፍቶላቸው የማስታወቂያ ባለሙያ ሆኖ የመስራት ዕድልን እንደከፈተላቸው ጠቅሰው ነበር።

ኦሊምፒክ እና አቶ ፍቅሩ

አቶ ፍቅሩ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ስለኦሊምፒክ ጨዋታዎች ያለው እውቀት እምብዛም ባልነበረበት ወቅት ውድድሩን ለአገሬው ለማስተዋወቅ መጽሐፍ እስከ ማሳተም ደርሰው ነበር።

“የኦሊምፒክ ጨዋታ የሚል መጽሐፍ በ1960 አሳተምኩ። ይህን መጽሐፍ ያዘጋጀሁት ሕዝቡ ስለ ኦሊምፒክ ጨዋታዎች እውቀት እንዲኖረው ነው።”

ይህን መጸሐፍም ለትምህርት ሚኒስቴር በመስጠት በአገሪቱ ባሉ ትምህርት ቤቶች እንዲታደሉ በማድረግ ወደ ወጣቶች እንዲደርስ አድርገዋል።

አቶ ፍቅሩ ከስፖርት ጋር በተቆራኘው ሕይወታቸው በበርካታ ኃላፊነቶች ላይ አገልግለዋል። በኢትዮጵያ የወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ ተቀጥተው የኢትዮጵያ የብስክሌት ፌዴሬሽን፣ የቴኒስ ፌዴሬሽን፣ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

አቶ ፍቅሩ የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበርን አቋቁመው የማኅበሩ ፕሬዝዳንት በመሆንም ሠርተዋል።

ከኢትዮጵያም ውጪ አቶ ፍቅሩ ከኦሊምፒክ ውድድር ጋር ባላቸው ቁርኝት ትልቅ የሥልጣን ደረጃ ላይ መድረስም ችለው ነበር።

ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ አቶ ፍቅሩ የመጀመሪያው ጥቁር የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ እና የፕሬዝዳንቱ ልዩ አማካሪ ሆነው ተሹመው እንደነበረ ይገራሉ።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የፕሬዝዳንቱ ልዩ አማካሪ፣ የአፍሪካ የሰፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር ዋና ፀሐፊ በመሆን አገልግለዋል።

የፊፋ የፕሬስ ኮሚቴ አባል የነበሩ ሲሆን እንደ ቢቢሲ፣ የአሜሪካ ድምጽ፣ ሬዲዮ ፍራንስ ኢንተርናሽናል ላሉ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎችን ይሰሩም ነበር።

ጋሽ ፍቅሩ ኪዳኔ የፒያሳ ልጅ ከጥቂት ዓመታት በፊት 
ፓሪስ በሚገኘው ቤታቸው ተቀብለውኝ  በሙያቸው፣ 
በእውቀታቸው፣ በፍቅራቸው ለሃገራቸው ለኢትዮጵያ እና
 ለኢትዮጵያውያን ካበረከቱት ከታሪካቸው በጥቂቱ ጨልፈው አጫውተውኝ ነበር አዜብ ወርቁ

የዛሬ 6 ዓመት ከጋሽ ፍቅሩ ኪዳኔ ጋር ሩዋንዳ ኪጋሊ ሻይ ጠጡበት ብለው ለእያንዳንዳችን 50 ዶላር ሰጥተውን ነበር ሰይድ ኪያር


ጋሽ ፍቅሩ ኪዳኔ ከስፓርት ጋዘጠኞች ዬናስ ተሾመ እና አረጋ ከፈለው

ጥር 17፡2008 ዓ.ም ከጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ ጋር የተደረገ ቆይታ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር



ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ SBS Amharic 

Life and Legacy: Fikrou Kidane – Pt 1 - SBS Amharic



Life and Legacy: Fikrou Kidane – Pt 2 - SBS Amharic

ፍቅሩ ኪዳኔ፤ በክፍል ሁለት የስፖርቱ መስክ ግለ-ሕይወት ትረካቸው፤ ከኮንጎ ዘመቻ ተሳትፎአቸው ተነስተው የቀድሞው የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚደንት ኹዋን አንቶኒዮ ሳማራንች ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ዘመናቸው ድረስ ያወጋሉ።


Life and Legacy: Fikrou Kidane – Pt 3 - SBS Amharic

ፍቅሩ ኪዳኔ፤ የአፓርታይድ አገዛዝ የዓለምን ኅሊና እየሞገተ በነበረበት ወቅት በስፖርቱ ዘርፍ እንደምን የፀረ-አፓርታይድ ትግሉ አካል ለመሆን እንደበቁ፤ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የስፖርት ተጠሪ ሆነው ከኔልሰን ማንዴላ ጋር እንደተገናኙ፤ በዓለም አቀፍ የሚዲያ አውታሮች እንዴት እንደሠሩ፤ ስለ አቶ ይድነቃቸው ተሰማና የውቤ በረሃ ትዝታዎቻቸውን አካትተው ያነሳሉ።



ሔኖክ ያሬድ

http://www.danielkibret.com/2010/11/blog-post_21.html

https://ghion-meg.com/2021/09/03/%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%8D%8D%E1%89%85%E1%88%A9-%E1%8A%AA%E1%8B%B3%E1%8A%94/

https://amharic.voanews.com/a/ethiopian-fikru-kidane-honored-with-sport-award-for-his-contribution-in-athletics/3276632.html

http://www.tadias.com/index.php?s=60th

https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2018/23368.html

https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2022/32933.html

https://ethiopiazare.com/amharic/images/doc/pdf/books/2011/1105ye-piassa-lij-by-mesfin-mammo.pdf


********************************

ምንጭ:-- https://www.bbc.com/amharic/articles/cx76v13n28eo 



Thursday, September 29, 2022

"የማሽላው አባት!"__ ተመራማሪ እና የዓለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኢጀታ

 

ዓለም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሰሩት ሥራ በአለም መድረክ ስማቸውንና የሀገራቸውን ስም ያስጠሩ ፀኃፊ፣ አርታኢ፣ መምህር፣ አማካሪ እና ተመራማሪ የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታን ከረጅሙ የሂወት ጉዞአቸው በጥቂቱ ይዘንላቹ ቀርበናል፡፡

ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ከአዲስ አበባ ስልሳ ሁለት ኪሎሜትር በስተ ምእራብ እርቀት ላይ በምትገኘው ኦሎንኮሜ በ1950 እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር ተወለዱ፡፡ የቄስ ትምህርታቸውን በአካባቢያቸው ሲከታተሉ ቆይተው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት በአካባቢያቸው ስላልነበረ 20 ኪሎሜትር በግራቸው ተጉዘው ተከታትለዋል፡፡



የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጅታ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጅማ የግብርና ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ የተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በእፅዋት ሳይንስ ከአለማያ ኮሌጅ በ1973 ዓ.ም ወስደዋል፡፡ እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ1976 በእፅዋት ሳይንስ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በ1978 በእጽዋት ማዳቀል እና ዘረመል ኢንጂነሪንግ አሜሪካ ከሚገኘው ፔድሩ ዩኚቨርስቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡

ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጅታ ከሁለት መቶ በላይ የጥናት ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን አራት መፅሐፎችን የአርትዎት ስራ ሰርተዋል፡፡

ላለፉት 28 አመታት በአሜሪካ በሚገኘው ፔድሩ ዩኚቨርስቲ ያገለገሉት የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ዩኒቨርስቲው አሉኝ ከሚላቸው ተመራማሪዎችም አንዱ ናቸው፡፡ ዶክትሬታቸውን ከተመረቁ በሆላ ወደ ሱዳን በመሄድ ማሽላ ላይ ምርምራቸውን ቀጥለዋል፡፡ በምርምራቸውም ድርቅን መቋቋም የሚችል የማሽላ ዘርያ ለአለም ማህበረሰብ ማበርከት ችለዋል፡፡ በ150 እጥፍ ምርታማነትን የሚጨምር የማሽላ ዝርያን ለአለም አበርክተዋል፡፡ ድርቅን መቋቋም የሚችል የማሽላ ዝርያ ላይ ባስገኙት ውጤት ከአምስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ አፍሪካዊያን የምግብ ዋስትንን ማረጋገጥ ችለዋል፡፡



ጥናታቸው በዚህ ሳያበቃ በአፍሪካ ምርታማነትን በ40 በመቶ የሚቀንሰው እስትራጋ የሚባለውን አረም መቋቋም የሚችል የተሸሻለ የማሽላ ዝርያን ኢትዮጲን ጨምሮ ለ12 አፍሪካ ሃገሮች ማቅረብ ችለዋል፡፡
ለእነዚህ እና መሰል የምርምር ስራዎቻቸው ከ17 በላይ አለም አቀፍዊ ፣ ሀጉራዊ እና ሀገራዊ ሽልማቶችን አግኝተዋል፡፡ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2009 ወርልድ ፉድ ኖብል ፕራይዚ የተሸለሙ ሁለተኛው አፍሪካዊ ለመሆን በቅተዋል፡፡ በአፍሪካ ናሽናሊቲ ሳይንስ ሂሮ ሽልማት ከተሸለሙ አፍሪካዊ ሰባት ተመራማሪዎችም አንዱ መሆን ችለዋል፡፡

ከሰባ በላይ አለም አቀፍ እና ሀገራዊ ተቋሞች በተለያዩ የሀላፊነት ደረጃዎች ላይ የሰሩት የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የአለም ህዝብ ቁጥር በጨመረ ቁጥር የምግብ ፍላጎት እየጨመረ ይመጣል ይህን ለመቋቋም ሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና የምርምር ፈጠራ ውጤቶች በመጨመር ይሄንን መቋቋም የግድ የሚል ነው ይላሉ፡፡ ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2011 በፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ የአለም አቀፍ የምግብ እና ግብርና ልማት ቦርድ ውስጥ እንዲሁም ከ2014 ጀምሮ በዩናይትድ ኔሽን ሴክሬተሪ ጄነራል ባኒኪሞን የዩዔን የሳይንስ አማካሪ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡


SOURCE:- Technology and Innovation Institute, Ethiopia

Tuesday, September 13, 2022

መስከረም ፩ ቀን ለምን የዘመን መለወጫ ሆነ?

~ የአመቱ ወራት ~

ጨለማው ሲጠፋ ዝናቡ ሲያቆም ፥
ያ የለውጥ ወራት መጣ መስከረም
ሰዎች ይነሣሉ ሊሰሠሩ ታጥቀው ፥
መስከረም ነውና ብርሃን ሰጭው ።
ብዙ እህል እሸት ጥቅምት ሲገባ ፥
ሜዳውና ጋራው አጊጦ ባበባ ፥
ህዳር ወር ደርቆ እረገፈ አበባ ፥
የኑግ ፥ የጎመን ዘር የሰሊጥ የተልባ ።
ታኅሣሥ እኩል ነው አዋቂና ልጁ ፥
ሊሠራ ይነሣል ሁሉም በየደጁ ።
ጥር ነው ወራቱ ያጨዳው ክምሩ ፥
ምርትን ለመሰብሰብ ያለው ግርግሩ ።
የካቲት መውቂያ ነው ክምሩ ፈረሰ ፥
ገለባው ተለየ ንፋሱ ነፈሰ ።
መጋቢት መጣልን ዓመት ተጋመሰ ፥
መጋቢት ወራት ሄደ እየቀነሰ ።
ሚያዝያ ተተክቶ መጋቢት አለፈ ፥
በልጉ ዝናብ ጣለ እያርከፈከፈ ።
ግንቦት ደረቅ ወር ነው ፀሐይዋ ከረረች ፥
አቧራው ቦነነ መሬት ተራቆተች ።
ሰኔ ደግሞ መጣ ክረምት አስከትሎ ፥
ገበሬው ተነሣ ማረሻውን ስሎ ።
ሐምሌም ተከተለ ገባ ዝናም ጭኖ ፥
ቀንና ሌሊቱን በዝናብ ጨፍኖ ።
ነሐሴ ተተካ ኅይለኛው ክረምት ፥
ያወርደው ጀመረ የዝናብ መዓት ።
አምስት አምስት ቀን ሦስቱን አመታት ፥
ባራተኛው አንዴ ስድስት ቀን ያላት ፥
መሸጋገሪያዋ የጳጉሜ ወር ናት ።
===============
ምንጭ 📖 ገፅ ፴፬ የ ፫ኛ ክፍል የአማርኛ መፅሃፍ


መስከረም 1 ቀን ለምን የዘመን መለወጫ ሆነ?
መስከረምና የዓመቱ ወራት ትርጉማቸውስ?
ዘመን መለወጫ ለምን መስከረም ወር ላይ እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ሲያትቱም ብርሃናት/ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜን ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱም ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱንም ጠንቀቀው ቢቆጥሩት 364 ቀናት ይሆናል፡፡ ለዘመን መታወቂያ ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ፈጠረ ይላልና /ሔኖክ.21.49/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ዓለምን ውኃ አጥለቅልቋት ከቆየ በኋላ ዳግመኛ ከነበረው ውኃ የተገለጠችበት ወር «በመጀመሪያም ወር በምድር ታየች የንፍር ውኃው ከምድር ደረቀ» የሚለውን መሠረት አድረገው የአቡሻኽር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስረዳሉ፡፡/ኩፋ.7.1/
በመሠረቱ ዘመን ተለወጠ ሲባል የሚለወጡት ወራቱ ብቻ አይደሉም፡፡ በወቅቱ የሚከሰቱት/የተከሰቱት/ መልካምም ሆነ ክፉ ነገር /ገጠመኝ/ ሲሆን ወራቶቹ ግን ያው በየዓመቱ እየተፈራረቁ ይመጣሉ፡፡ ዘመን መለወጫ ላይ የሰው ልጆች ሕይወት ሊለወጥ ይገባል፡፡ ተማሪው ተምሮ ወደቀጣዩ ክፍል /ደረጃ/ የሚለወጥበት፣ ገበሬው የክረምቱን ወራት በሚገባ ተጠቅሞ የሚቀጥለውን የበጋ ወራት የሚቀበልበት፣ ሠራተኛው የክረምቱን ዝናብ ታግሶ የፀሐይን ወራት የሚቀበልበት ሌላውም እንደዚያ ሆነው ወራቶቹ በዚያ ዘመን ያለው የተፈጥሮ ክስተቶች የሚለወጥበት ዘመን ተለወጠ እየተባለ ይነገራል፡፡
የቀመር መጀመሪያ የሆነው ዕለት ማክሰኞ ሚያዝያ 1 ቀን ነው። ነገር ግን የሚያዝያን እንዳንጠቀም መዓልቱና ሌሊቱ እኩል አይደለም፡፡
ይህን ተከትሎ በሚዞር ነገር መስማማት እንጂ ሁሉም መነሻ ሆኖ ማገልገል ይችላሉ፡፡ ለመስማማት ደግሞ በቂ ምክንያት ያስፈልጋል፡፡ሊቃውንት ደግሞ ብዙ ምክንያት ያለው መስከረም ስለሆነ መነሻቸው በመስከረም እንዲሆን አድርገዋል፡፡ የመጻሕፍት መምህራን ሌላ ምክንያት ይጨምራሉ፡፡ እስራኤላውያን ከግብጽ በወጡበት የሰባተኛው ወር መባቻ እንደሆነ እግዚአብሔር አዝዟል፡፡ ይኸውም መስከረም ነው ይላሉ፡፡ ክረምት በጨለማ በብሉይ ይመሰላል ፀሐይ የሚወጣበት መስከረም ደግሞ በብርሃን በሐዲስ ኪዳን ይመሰላል፤ ስለዚህ ለዓውደ ዓመት መነሻ ወር መስከረም ነው፡፡

የኢትዮጵያውያን የዘመን መለወጫ መስከረም ነው፡፡ መስከረም 1 ቀን ርእሰ ዓውደ ዓመት ተብሎ ይጠራል፡፡ ትርጉሙም ርዕስ የአንድ ጽሑፍ /ንግግር በር እንደሆነ ሁሉ በዓመት ውስጥ ያሉ ዓውደ ዓመቶች /በዓሎች/ እና አጽዋማት ማወቂያ /ማመላከቻው/ መስከረም 1 ቀን የሚውልበት ነውና፡፡ እንዲሁም የዓመቱ በዓላትና አጽዋማት የሚታወጀው መስከረም 1 ቀን ነው፡፡ በዚሁም ዕለት መዓልቱን /በፀሐይ/ ሌሊቱን /በጨረቃ/ በመቁጠር ምሥጋና ለእግዚአብሔር ይቀርባል፡፡
መስከረም ማለት ምን ማለት ነው ? የመስከረም ወር ትርጓሜስ?
መስከረም ማለት ከግእዝ የመጣ ቃል ሲሆን (ከሪም- ወይም ከሪሞት)
(መዝከረ-ውይም -ከረም) ከሚሉ የግእዝ ቋንቋዋች የተገኘ የውህድ አረፍተ ነገሮች ውጤት ነው ።
1️⃣ ከሪም ወይም ከሪሞት ማለት ምን ማለት ነው ?
ከሪም ወይም ከሪሞት ማለት-በግእዝ የከረመ፣ የቆየ የሰነበተ ማለት ሲሆን ይህም የክረምት ቆይታ የሚገልፅ እና የክረምት መገባደጃ እንደሆነ የሚያመለክት ነው በሌላ ፍቺ የከረመው ክረምት ማለቂያ የመፀው መባቻ መጀመሪያ ማለት ነው ።
2️⃣ ሌላው ደሞ መዝከረ - ከረም ከግእዝ ቃል የተገኝ ቃል የተገኝ ውህድ ሲሆን ትርጓሜውም መዝከር ማለት በግእዝ መዘከር፣ ማስታወስ፣ ማሰብ ማለት ነው።
ከረም ማለት ደሞ የቆየ፣ የከረመ፣ የሰነበተ ማለት ሲሆን በአጠቃላይ
መዝከረ ከረም ማለት የከረመን የቆየን መዘከር ማስታወስ ማለት ነው
ለዚህም ሲባል የቆየውን አመት የምንዘክርበት አዲሱን ዓመት የምንቀበልበት ወር ለማለት መዝከ ከረም(መስከረም) እንለዋለን። በዚህም ምክንያት አውደ ዓመት አዲስ ዓመት ሆነ የከረመውን የቆየውን አሮጌውን ዓመት ተሸኝ የምንቀበልበት ሰናይ ወር መስከረም ሆነ አሮጌው የቆየው ክረምት ተሸኜ ማለት ነው።
መዝከ ከረም ወደ አማርኛ ሲመለስ አንዱን ከግእዝ በመተው
መስከረም ወደሚል አማርኛ ተቀይሮ ይጠራል። የወራቶች መጀመሪያ የአዲስ ዓመት መባቻ የክረምት መገባደጃ ለማለት መስከረም ተባለ።

13ቱ የኢትዮጵያ ወራት አሰያየም
1️⃣. መስከረም
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - መስ እና ከረም ሲሆን
ትርጉሙም መስ፣ አለፈ፤
ከረም፣ ክረምት ማለት ሲሆን፤ መስከረም ማለት ክረምት አለፈ ማለት ነው።
2️⃣. ጥቅምት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ጠቀመ።
ትርጉም ሠራ፣ ጠቃሚ ጊዜ ማለት ነው።
3️⃣. ኅዳር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ - ኀደረ።
ትርጉም አደረ፣ ሰው በወርሃ አዝመራ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ይገልፃል።
4️⃣. ታኅሣሥ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ኀሠሠ።
ትርጉም መረመረ፣ ፈለገ፣ በመኽር ወቅት የሰብል ምርመራ ያመለክታል።
5️⃣. ጥር
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ነጠረ።
ትርጉም ጠረረ፣ ብልጭ አለ፣ ነጻ በራ የፀሀይን ግለት ወቅት ያሳያል።
6️⃣. የካቲት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ከቲት።
ትርጉም (የእህልን) መክተቻ ማለት ነው።
7️⃣. መጋቢት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ መገበ።
ትርጉም በቁሙ የሚመግብ (በጎተራ የተከተተው የሚበላበት) ማለት ነው።
8️⃣. ሚያዚያ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ መሐዘ።
ትርጉም ጎረመሰ ጎበዘ ሚስት ፈለገ(ወርኀ ሰርግ መሆኑን ሲያጠይቅ)
9️⃣. ግንቦት
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ገነበ።
ትርጉም ገነባ፣ ሰራ፣ ቆፈረ፣ ሰረሰረ (ለእርሻ የመሬቱን መዘጋጀት ያሳያል።
1️⃣0️⃣. ሰኔ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ሰነየ።
ትርጉም፣ አማረ ማለት ነው።
1️⃣1️⃣. ሐምሌ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ ሐመለ።
ትርጉም ለቀመ(ለጎመን)
1️⃣2️⃣. ነሀሴ
የግእዝ ሥርወ ቃሉ አናህስየ።
ትርጉም አቀለለ፣ ተወ የክረምቱን እያደረ መቅለሉን ያመለክታል።
1️⃣3️⃣. ጳጉሜን
ሥርወ ቃሉ ግሪክ ሲሆን ኤጳጉሚናስ።
ትርጉም ተጨማሪ ወር ማለት ነው ።
መልካም አዲስ ዓመት ‼

https://www.facebook.com/petros.kebede




ለምን መስከረም? – ለምን ዕንቁጣጣሽ?


“መስከረም በአበባው ሠርግ በጭብጨባው ይታወቃል” ነው የሚባለው

  • ለንጉሥ ቢኾን ኑሮ “ዕንቁ ፃዕፃኹ” ይባል ነበር እንጂ ዕንቁጣጣሽ አይባልም ነበር  

ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ፣ የመሸጋገሪያው ዕለት “ቅዱስ ዮሐንስ” እየተባለ ሲጠራ፣ በባህላዊና ትውፊታዊ መዘክሩ ደግሞ “ዕንቁጣጣሽ” በመባል ይታወቃል፡፡ ሁለቱም ማለትም ቅዱስ ዮሐንስ እና ዕንቁጣጣሽ መስከረም ፩ ቀን ተደርገው ሲዘከሩም፣ ሃይማኖታዊና ትውፊታዊ ትርጓሜያቸውን ይዘው እንደኾነ መዘንጋት የለበትም፡፡

ሃይማኖት ስንልም ብራና ፍቃ፣ ቀለም አውጥታ፣ ብርዕ ቀርጻ፣ ታሪክን፣ ፍልስፍናን፣ ቁጥርን፣ የሀገር ፍቅርን፣ ነፃነትን፣ ጀግንነትን – መምህርቷ የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ማለታችን እንደኾነ ይታወስልን፡፡ እንግዲህ መስከረም ፩ ቀን ለእኛ ኢትዮጵያውያን የዘመን መለወጫ ወይም ወደ አዲስ ዓመት ተሸጋገርንበት ስንል፣ አዲስነቱ እንዲታወቅ እንደ መጽሐፉ ሥራት፣ እንደ ሊቃውንቱ ትምህርት የገበየነውን ለማካፈል ነው፡፡ ከነይትበሃሉም “መስከረም በአበባው ሠርግ በጭብጨባው ይታወቃል” ነው የሚባለው፡፡

ለምን መስከረም? መስከረም የጨለማው (ክረምት ለማለት) ጊዜ አልፎ ብርሃን የሚታይበት፣ ዕፅዋት፣ አዝርዕት፣ አታከልት፣ የሚያብቡበት፣ የሚያፈሩበት፣ እንስሳት የጠራ ውሃ እየጠጡ፣ ለምለም ሣር እየነጩ የሚቦርቁበት፣ በአጠቃላይ መሬት በልምላሜ አጊጣ፣ ተውባ የምትታይበት በዚሁ በወርኀ መስከረም ነው፡፡ አንዳንድ መምህራንም መስከረምን “የወራት ፊታውራሪ” ይሏታል፡፡

የአቡሻኸር ሊቃውንት እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረው መስከረም ፩ ቀን ነው ሲሉ ያትታሉ፡፡ ሌሎቹም መስከረም በኢትዮጵያ ብቻ ሳይኾን፣ ከዘመነ ሥጋዌ በፊት በዓለም ኹሉ የወርና የዓመት መጀመሪያ እንደነበር ይገልጹና የክረምት ጫፍ መጨረሻ፣ የመፀው መባቻ ከመኾኑም በላይ መዓልቱና ሌሊቱ ትክክል የሚኾንበት ወር ነው ይሉታል፡፡ በነገራችን ላይ መስከረም፡- ከረመ ከሚለው ግስ የተገኘ፣ ትርጓሜውም ቀዳማይ፣ ለዓለም ኹሉ መጀመሪያ፣ ርዕሰ ከራማት፣ መቅድመ አውራኅ ማለት እንደኾነ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡

መስከረም ሌላም አብነት አለው፡፡ “ርዕሰ-ዓውደ ዓመት”፣ “ዕንቁጣጣሽ” የተባሉትን ምሥጢራት ተሸክሟል፡፡ የምሥጢር አባቶቻችንም ይህንን በአፍም በመጽሐፍም ሲነግሩን ዘመናትን አስቆጥረዋል፣ ነገም እንዲሁ ነው፡፡ እና ለምን መስከረም? ለምን ዕንቁጣጣሽ? በሚሉት ጥያቄዎች ዙሪያ የሊቃውንቱን የቃልና የጽሑፍ አስረጅ እንደሚከተለው እናየዋለን፡፡ የመጀመሪያው አፈሊቅ አክሊሉ ገብረኪሮስ ናቸው፡፡

ሊቁ የኢትዮጵያ ጋዜጦችና መጽሔቶች አቋማቸውን የሚገልጹበትን ቦታ “ርዕስ አንቀፅ” በሚል ስያሜ እንዲጠራ ያደረጉ ዜና ቤተክርስቲያን እና በኋላም የአዲስ ዘመን ጋዜጠኛ የነበሩ ናቸው፡፡ ያልጻፉት ታሪክ፣ የማያውቁት ትውፊት እና ያልተቀኙት የቅኔ ዓይነት የለም ማለት ይቻላል፡፡ ምሉዕ በኩለሄ፡፡

እኚሁ ሊቅ ታዲያ ከዛሬ 56 ዓመት በፊት፣ ማለትም በ1955 ዓ.ም በዚያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ስለዘመን መለወጫና ዕንቁጣጣሽ ሲተርኩ፣ “ስለዕንቁጣጣሽ በቃል የተነገረ እንጂ በጽሑፍ የሠፈረ አልተገኘም” ነው ያሉት፡፡ ኾኖም አሉ፤ “…ኾኖም በቃል ሲወርድ ሲወራረድ እንደመጣ ‹ዕንቁ› ብሎ ‹አዕናቁ› ከግእዝ የተወረሰ ቃል ነው፡፡ ዕንቁ ለአንድ፣ አዕናቁ ለብዙ ይነገራል፡፡ ጣጣሽ፡- “ፃዕፃዕ” ከሚለው የግእዙ ቃል የተወረሰ ነው፡፡ በአማርኛ ጣጣ፣ መባዕ፣ ግብር፣ መፍቀደ፣ በረከተ-ገጽ ማለት ይኾናል፡፡ መጽሐፍተ ብሉያት ወደ እግዚአብሔር የሚቀርበውን መባዕ፣ የሚገባውን ግብር “ፃዕፃዕ” ይሉታል፡፡ በየዓመቱ ዕንቁጣጣሽ ማለታችን “የዕንቁጣጣሽ ግብር፣ የዕንቁጣጣሽ በረከተ-ገጽ ነው ብለን የምሥራች ማሰማታችን ነው፡፡

በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዕንቁጣጣሽ የተበረከተው፣ ለቀዳማዊ ሚኒሊክ እናት ለንግሥት ማክዳ ነው፡፡ ንግሥት ማክዳ ቀዳማዊ ሚኒሊክን በወለደች ጊዜ ሕዝቡ “ንጉሥ ተወለደ” ብሎ ዕልል ዕያለ፣ የአበባ ዕንቁጣጣሽ ለንግሥት ማክዳ አበረከተ፡፡ ዕንቁጣጣሽ መባሉም መጀመሪያ ለንግሥቲቱ ስለተገበረ ነው፡፡ ለንጉሥ ቢኾን ኑሮ “ዕንቁ ፃዕፃኹ” ይባል ነበር እንጂ ዕንቁጣጣሽ አይባልም ነበር፡፡ በሸዋም ሕዝቡ ግብር አለብኝ ሲል “ጣጣ አለብኝ” ይላል፡፡ ከዚህም በቀር ንጉሥ ሰሎሞን፣ ከደስታው ብዛት የተነሣ ለንግሥቲቱ፣ አስቀድሞ ለጣትሽ መታሰቢያ ይኹንሽ ብሎ የዕንቁ ቀለበት ሰጥቷት ነበር እያሉ ሊቃውንቱ ነግረውናል …” ብለዋል፡፡

ሌሎችም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት፣ ስለዕንቁጣጣሽ፣ ስለመስከረም እና ዘመን መለወጫ ምሥጢር፣ ከሃይማኖታዊ ትርጓሜው ባሻገር ከሥነ-ቃል ወይም አፍኣዊ ኪነተ ቃል አኳያ አያሌ መጣጥፎችን አኑረውልን አልፈዋል፡፡ በዚህ ረገድ አለቃ አያሌው ታምሩ /ነፍስ ሔር/ ምንጊዜም ሲታወሱ፣ እንደ መምህር ሀብተ ማርያም ተድላ፣ እንደ አለቃ ነቢየ ልዑል ዮሐንስ /ነፍስ ሔር/ እና ቀሲስ ልሳኑ በዛብህ /ነፍስ ሔር/ የምንጠራቸው መምህራነ ቤተክርስቲያን ናቸው፡፡

አለቃ ነቢየ ልዑል ደግሞ ስለዕንቁጣጣሽ ሲተርኩ፣ “ዕንቁጣጣሽ ግጫ ማለት ነው” ይላሉ፡፡ “ግጫ ደግሞ የሣር ዓይነት ነው፡፡ የአበባ እርጥብ ስጦታ መስጠት የተጀመረው በኖኅ ዘመን ነው፡፡ ኖኅ የጥፋት ውሃ በጎደለ ጊዜ፣ መጉደሉን ለማረጋገጥ ርግብን ልኳት የወይራ ቅጠል አምጥታለች፡፡ እርሱም የመርከቡን ጣራ አንስቶ ከወጣ በኋላ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት በማቅረብ፣ ልዩ ልዩ ጸዐዳ ሽታ ያላቸውንም አበቦች አቅርቧል፡፡ ንግሥት ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ዘንድ ስትኼድ አምስት መቶ ደናግል ተከትለዋት ነበር፡፡ የእልፍኝ አሽከሮቿም እነሱ ሲኾኑ አበባውም የዕንቁጣጣሹም አሰጣጥ በእነሱ ተፈጽሟል፡፡ ስለዚህ ዛሬ ልጃገረዶች አበባ ቀጥፈው፣ እንግጫ ነቅለው፣ ሸልመው የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ይህም በአበው ዘንድ ሲያስመርቃቸው፣ በጎረምሳው ዘንድ ደግሞ የመታጨት ዕድል ያስገኝላቸዋል …” ነው ያሉት፡፡

በነገራችን ላይ ከላይ የጠቀስኳቸው ሊቃውንት፣ ከአለቃ አያሌው በስተቀር ቤተክርስቲያኗ በምታሳትማቸው መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ ሲጽፉ የነበሩ ዓምደኞች እንደነበሩ ላስታውሳችሁ፡፡ እናም ከዛሬ አርባና ሃምሣ ዓመታት በፊት፣ በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሰፈሯቸው መጣጥፎች፣ በመስኩ ጥናትና ምርምር ማድረግ ለሚፈልጉ የጥንታዊ መዛግብትና ኪነቃል ተማሪዎች ግሩም የኾነ ምንጭ እንደሚኾኗቸው እጠቁማለሁ፡፡

እኔም ታዲያ፣ አለቃ አያሌው ታምሩን /ነፍስ ሔር/ መላልሼ ከጠየቅኋቸው ልዩ ልዩ ጉዳዮች መካከል፣ ለዘመን መለወጫ እና ዕንቁጣጣሽ ከ20 ዓመት በፊት “ጦማር” ጋዜጣ ላይ የጠየቅኋቸው ነው፡፡ እርሳቸውም ስለታሪኩ፣ “የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕገጋት” የተሰኘ መጽሐፋቸውን ጠቅሰው ያስረዱኝ የሚከተለው ነው፡፡ “የዘመን መለወጫ የታወቀው በሦስት ዓይነት ነው፡፡

አንደኛ እስራኤል በብሉይ ኪዳን ያከብሩት የነበረው ሚያዚያ ፩ ቀን፣ ሁለተኛ የዓለም ክርስቲያን የክርስቶስን ልደት ተቀዳሚ በማድረግ የሚያከብሩት ጥር ፩ ቀን፣ ሦስተኛ ኢትዮጵያ ጥንተ መሠረትነቱን አውቃ የምታከብረው መስከረም ፩ ቀን ነው፡፡ እስራኤል የዘመን መለወጫ በዓልን በሚያዚያ ማድረጋቸው፣ በዚህ ወር ከግብፅ ባርነት ነፃ ስለወጡና እግዚአብሔር ይህንን የነፃነት በዓል በየዓመቱ እንዲያከብሩት ስለአዘዛቸው ነው፡፡ የዓለም ክርስቲያን ጥር ፩ ቀን ማክበራቸው የክርስቶስን ልደት ምክንያት በማድረግ መኾኑ የታወቀ ነው፡፡

ኢትዮጵያ መስከረም ፩ ቀን የምታከብረው ዘመን መለወጫ የተቀበለችው ከካም ነው፡፡ የተጀመረበትም ካምና ልጁ ኩሳ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበት፣ አኵሱም በኩሳ ስም የተመሠረተችበት ጊዜ ነው፡፡ ዘመኑም በኢትዮጵያ ላይ ከ4 ሺህ 900 በላይ ሲኾን፣ ከጥፋት ውሃ በኋላ በኖኅ ዕድሜ 601 ጀምሮ 552 ዓመት አሳልፎ እነሆ ደርሰንበታል፡፡

ኖኅም ሲያከብረው፣ ጥንቱን ዓለም የተፈጠረበት ወር እንደመሆኑ መጠን ከአዳም ጀምሮ ወረደ፣ በአበው እየተላለፈ እስከ እርሱ የደረሰ መኾኑና ኋላም የቀላይ አፎች የተከፈቱበት፣ የጥፋት ውሃ መጉደል የተጀመረበት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጥፋት ውሃ ወዲህ ክረምትና በጋ መፈራረቅ የጀመሩበት፣ ምድር የፍሬ ጽንስ፣ አበባ መልክ ያሳየችበት ስለኾነ ነው፡፡ ፊተኛው ሲጨመር 7 ሺህ 452 ዘመናትን ማሳለፉ ነው፡፡ ስሙም በግእዝ “ርዕሰ-ዐውደ ዓመት”፣ በአማርኛ “ዘመን መለወጫ” “ዕንቁጣጣሽ”፣ “ቅዱስ ዮሐንስ” እየተባለ ይጠራል፡፡

ርዕሰ-ዐውደ ዓመት ማለት፣ የዘመን መለወጫ መጀመሪያ፣ ዕንቁጣጣሽ ማለት “ዕንቁ ዕጽ አወጣሽ ብሎ የአበባውን መፈንዳት ወይም “ዕንቁ ዕጣ ወጣሽ” ብሎ፣ መልካሚቱ ምድር ኢትዮጵያ በዕጣ ለካም መድረሷን የሚያመለክት፣ ቅዱስ ዮሐንስ ማለት፣ በዓሉ ከመጥምቁ ዮሐንስ ዕረፍት ጋር የተደጋገፈ መኾኑን ስለሚገልጥ ነው፡፡

… መስከረም ማለትም፣ እግዚአብሔር ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ ድረስ ሞልቶ የነበረውን ውሃ ከሦስት ከፍሎ በጠፈር፣ በሐኖስ፣ በውቅያኖስ ከወሰነ በኋላ ደረቁ ይገለጥ ባለ ጊዜ ምድር ገብሬ አርሶ፣ አለስልሶ እንዳከተማት ሁሉ፣ ለዘር የተመቸች ኹና ተገኝታ ነበርና፣ መሀሰ ቆፈረ ከረመ- ከረመ የሚሉትን ሁለቱን ግሶች በማቀነባበርና በማስተባበር መስከረም አጥብቆ፣ ታርሶ፣ ከረመ እንደ ማለት፣ ስሙን ከግብሩ ነስቶ የሚጠራበት ነው፡፡

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም አታሚን – አታኒም የተባለውን ቃል ሲተረጉሙ፣ አታን ወይም ኤታን ማለት ጥንተ ፍጥረት እንደኾነ ዕብራይሰጢውን በማዋሐድ ገልጠው፣ ይኸውም በዕብራውያን ሰባተኛ ወር ጥቅምት፣ በኢትዮጵያውያን በፀሐይ አቆጣጠርና በአቡሻኸር ጠንቃቃ ቁጥር ግን መስከረም መኾኑን አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአኵሱም መዲናነት የተቀበለችውና ስታከብረው የምትኖረው መስከረም ፩ ቀን የሚውለው፣ ርዕሰ-ዓውደ ዓመቷ የኩሽ ኩሳ መዲናና መቃብር በመኾኗ፣ አኵሱም ርዕሰ አኅጉር ኩሺ /ኩሳ/ አሞን ለአኅጉረ ኩሺ /ኩላ/ ተብላ የምትጠራውን አኵሱምን /አኩሺምን/ ያህል ጥንታዊነቷን ሲመሰክር የሚኖር ነው፡፡ በዓመተ ዓለም፣ በዓመተ ኩነኔ፣ በዓመተ ምሕረት ደመራ፣ ዘርዝራ፣ ዐጥፋ፣ ነጥላ፣ ጠቅልላ፣ ከፍላ የምትሰጠው የዘመን ቁጥርም የጥንትነቷ ፍሬ ነው” ብለዋል አለቃ አያሌው፡፡

እንግዲህ ተደጋግሞ እንደሚገለጸውና እንደሚታወቀውም፣ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መኾኑ ነው፡፡ ካስማዋም ከአዳም እስከ ልደተ ክርስቶስ አምስት ሺህ አምስት መቶ የሚለው ኾኖ፣ በ550፣ ክርስቶስ ተወለደ ብላ እነሆ አሁን ፳፻፲፪ /ሁለት ሺህ አሥራ ሁለተኛው/ ዘመን ላይ መኾኗን ልብ ይሏል፡፡

https://ethio-online.com/archives/4924