ከደራሲያን ዓምባ

Friday, October 5, 2012

ምርጥ አባባሎች

''' ምርጥ አባባሎች'''


• በአንድ ሰው የማስታወሻ መያዣ ደብተር ውስጥ ቦታ ማግኘት ይቻላል፡፡ ነገር ግን በልቡ ውስጥ ቦታ ማግኘት ችግር ነው፡፡
• ሕጎችን ማውጣት ቀላል ነው መተግበር ግን ችግር ነው፡፡
• በየዕለቱ ማለም ቀላል ነው፡፡ ህልምን እውን ለማድረግ መታገል ግን ከባድ ነው፡፡
• ሙሉ ጨረቃን አይቶ ማድነቅ ቀላል ነው፡፡ የጨረቃን ሌላ ገጽታ ማየት ግን ችግር ነው፡፡
• ለአንድ ሰው አንድ ቃል መግባት ይቻላል፡፡ ቃልን መፈጸም ግን ችግር ነው፡፡
• ሌሎችን መውቀስ ይቀላል፡፡ ራስን ግን ይከብዳል፡፡
• አንድን ነገር ለማሻሻል ማሰብ ቀላል ነው፡፡ ማሰብን አቁሞ ወደ ተግባር መግባት ግን ጭንቅ ነው፡፡
• ሌሎችን በመጥፎነት መፈረጅ ቀላል ነው፡፡ ጥሩ ሊሆኑ ይችላሉ ብሎ ማሰብ ግን ከባድ ነው፡፡
• ፍቅር የሚጠይቀው ብቸኛ ስጦታ "ፍቅር" ነው፡፡ (ጆን ግሬይ)
• መሳሳት ሰብዓዊነት ሲሆን ስህተትን ማመን ግን ቅዱስነት ነው፡፡ (ዳፍ ባውርሰን)
• በሕዝብ ዘንድ አመኔታ ያለው ሰው ራሱን እንደ ሕዝብ ንብረት አድርጎ ይቆጥራል፡፡ (ቶማስ ጀፈርሰን)
• ወንዶች ሴቶችን የሚያፈቅሩትን ያህል ሰማያዊውን ዓለም ቢያፈቅሩ ኖሮ መላዕክት (አማልክት) መሆን በቻሉ ነበር፡፡ (ማልኮላም ኤክስ)

******************
ምንጭ:---(ምርጥነህ ታምራት፣ ጣዝማ፣ 1999)

-   የራስህ ቤተ መንግሥት ሁን፡፡ አለበለዚያ ዓለም እስር ቤትህ ትሆናለች፡፡ (ጀንደን)
-  ቅናት ሲመገብ ያደገ ፍቅር አሟሟቱ ከባድ ነው፡፡ (ዴቪድ)
-  ቅናትን እንደሳቅ የሚያስፈራው ነገር የለም፡፡ (ፍራንሷ ሳንጋ)
-  ቅናትን የሚፈጥረው ፍቅር ሳይሆን ራስ ወዳድነት ነው (ዋሊንግተን)
-  ከሞትክ አይቀር ደስ ብሎህ ሙት፡፡ (ቻርልስ ጀምስ ፊክስ)
-  ትዳር ያዙ ወይ የሞቀ ትዳር ይሆንላችሁና በደስታ ትኖራላችሁ፣ ወይም ጨቅጫቃ ትዳር ይሆንባችሁና ፈላስፋ ትሆናላችሁ፡፡ (ሶቅራጥስ)
-  ገበታህን በፍቅር ቅመም አሳምረው፡፡ ሁሉንም ሰሃን በደስታ ይሞላዋልና፡፡ (ዥን ኮክቶ)

***************************************************************

ምንጭ:---(ምርጥነህ ታምራት፤ጣዝማ የሚሊኒየሙ ምርጥ አባባሎች፣2000)

- የማያውቅ ማወቅንም የሚያውቅ ምሁር ነውና ተከተለው
- ለገዛ ራስህ ክቡር ዓላማዎች ታምኝ ሁን።
- የትምህርት ሁሉ ዓላማና ግብ ስብዕናን ማዳበር ነው።
- ማለዳ ስንነሳ ልብ እንበል? ከሐብት ሁሉ የሚልቁት 24 ሳዓታት የኛ ናቸው።
- ምንም ሳንሰራ ከምናሳልፈው ህይወት ስህተት እየሰራን የምንገፋው ህይወት የተሻለ ነው።
- የያውን ሁሉ ለመያዝ የሚሞክር አንድ ቀን እባብ ጨብጦ ይነደፋል።
- የቁም ነገር ጫፍ የሚባለው ሩቅ ያለውን መመልከት ሳይሆን በእጁ ያለውን መስራት ነው።-
- ስህተቱን ሲያውቅ ጩቤ የማይረግጥ ምሁር ምሁር ሊባል አይችልም።
- ነፃነት ስህተት የመሥራት መብትን ካላካተተ መኖር ፋይዳ የለውም።
- ሲጋራ በአካል ውስጥ የሚጓዝ የጫካ ውስት እሳት ነው።
- በዓለም ከፍተኛ መራራ ነገር ቢኖር ራዕይ አባል ሆኖ መፈጠር ነው።
- ባልና ሚስት በጋራ የሚተነፍስ ሳንባ ባይነራቸውም በጋራ የሚጓዝ የትዳር ሰንሰለት አላቸው።
- በዓለም ትልቁ ውርደት ከመስራት የሰው እጅ ማየት ነው።
- በአንድ ዛፍ የሚዘሉ ጉሬዛና ጦጣ አብረው ቢውሉም ተቃቅፈው አይተኙም።
- በኢላማህ የማትተማመን ከሆንክ ወደ ነብር አትተኩስ።
- በዛሬ ደስታ ብቻ የሚፈነድቁ ሰዎች ውብ አበባ ከተቀጠፈ መጠውለጉን የሚዘነጉ ናቸው።
- በፍቅር የተነሳ ልብ በፍቅር ይሰክናል።
- ብርቱካን መጨመቁን ቢያውቅ ውሃ አይዝልም ነበር።
- ብቃት የሚመጣው በውጥረት ሳይሆን በተግባር ምጥቀት ነው።
- ለማመን እንጂ ላለማመን ምክንያት አያስፈልግም::
- መልከመልካም ሴት ባየህ ጊዜ ተፈጥሮን አድንቅ እንጂ የዝሙትን መንፈስ አይሰማህ' ዝሙት ከደካማ መንፈስ የሚመንጭ ነው።
- እያንዳንዱ ይሕይወት ቀን ወደ ሞት የሚያደርስ ደረጃ ነው።
- ወደ ፊት የምንራመድ ከሆነ ታሪክን መድገም ብቻ ሳይሆን አዲስ ታሪክ መፍጠር አለብን።/መሀተመ ጋንዲ/ 

******************************************************************************
ምንጭ:---http://girmayreda.blogspot.com

15 comments: