ከደራሲያን ዓምባ

Monday, October 1, 2012

ከደራሲያን ዓምባ

  ሀዲስ ዓለማየሁ እና ስራዎቻቸው 

                ( ጥቅምት 7 ቀን 1902 ዓ.ም- ህዳር 26 ቀን1996 ዓ.ም)

ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዶዳም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በ ጥቅምት ፯ ቀን ፲፱፻፪ ዓ.ም. ተወለዱ። 
ሀዲስ ዓለማየሁ በርካታ የስነጽሑፍ ሥራዋችን አበርክተዋል። 
  1. ተረት ተረት የመሰረት -1948 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  2. ኢትዮጵያ ምን ዓይነት አስተዳደር ያስፈልጋታል? - 1953 ዓ.ም. ((ኢ-ልብ ወለድ))
  3. ፍቅር አስክ መቃብር - 1958 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  4. ወንጀለኛው ዳኛ - 1974 ዓ.ም. (ልብ ወለድ)
  5. የልም  ዣት - 1984 ዓ.ም.(ልብ ወለድ)
  6. የትምህርትና የተማሪ ቤት ትርጉም - 1948 ዓ.ም. (ኢ-ልብ ወለድ)
  7. ትዝታ - 1985 ዓ.ም. (ግለታሪክ )
  8. የአበሻና የወደኋላ ጋብቻ -  (ተውኔት)

 ሀዲስ ዓለማየሁ በኢትዮጵያ የስነ ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከታቸው 
በሥነ ጽሑፍ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሽልማት ድርጅት ተሸላሚ ፣
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክቶርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል ። 
ደራሲው በኅዳር 26 ቀን 1996 ዓ.ም. በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ።


 ምርጥ አባባሎች:-
  • " የትልቅ ሰውን ትልቅ ስራ ሌሎች ይናገሩለታል እንጂ እርሱ አይናገርም።" (የልም  ዣት)
  • " የምትወደው ሁልጊዜ ሲለይህ የሚያስረሳህ እንጂ የሚያስታውስህ  ነገር አትፈልግ ያለዚያ ህይወትህ የስቃይ ህይወት ይሆናል።" (ፍቅር አስክ መቃብር)
  • " ሰው ባለመብት የሚያደርገው የሚፈፅመው ተግባር ነው ተግባሩን ሳይፈጸም በመብቱ የተጠቀመ ሁሉ ባለዕዳ ነው።" (ወንጀለኛው ዳኛ)

No comments:

Post a Comment