ከደራሲያን ዓምባ

Monday, May 20, 2013

የግጥም ጥግ

የሰንበት ጽንስ
            ፊርማዬ ዓለሙ 
********************
በስራው ቀን ቀርቶ በተፈቀደበት፣
በእሁድ በቅዳሜ በሰንበት ሰርቼ ባል በተባለበት፣
ፈጣሪ ሥራውን ሁሉ ባበቃበት፣
በሰንበት ጸንሼ ባል በተባለበት።
ተዘፍዝፎ ቀረ ልጄ ከጅምሩ፣
ሲፈራረቅበት ውኃ፣ ጣይ፣ አየሩ።
እሱን እየማገ  እየተነፈሰ፣
ላቅመ ሔዋን በቃ ልቡ እንደፈሰሰ፣
ለሰንበት ጽንሶቹ አጅሬም ደረሰ።
የእሁድ ቅዳሜ ጽንስ በረከት የራቀው፣
ሰበዝ አልባ ውጥን ሲጀመር የሚያልቀው።
ቢመክሩት በጅ አይል የሚረዳው የለ፣
ተቀምጦ ለመኖር ብቻ ይታደለ።
የዕድሜውን አገዳ በተራ እየላጠ፣
ተዘፍዝፎ ቀረ ነገር እየበላ ወሬ እያላመጠ።
***************************
ምንጭ፡--አዲስ ዘመን ግንቦት 2005

No comments:

Post a Comment