ከደራሲያን ዓምባ

Monday, May 20, 2013

የግጥም ጥግ

"አበበ እንጂ መቼ ሞተ!!"
በሎሬት ፀጋየ  ገብረ መድኅን
******************

























በቅፅበት ፀንሶ ሞቱን
ድፍን አለም ደፍቶ አንገቱን
በልቡ ቀርፆት ፀሎቱን
በህሊናው ነድፎት ስሙን
በገፁ ፅላት ታሪኩን፡፡
አእዋፍን በደመና፣ ጀግናን በምድር ያስደነቀ
ማራቶን ጮራው ጠለቀ
በራሪው ኮከብ ወደቀ፡፡























 በቃ ጀግናው ተከተተ
ይኸው የማይሞት ሰው ሞተ፡፡
ብለን እንበል እባካችሁ፡- አበበ ጀግና ነውና
ተስፋ አይቀበርምና፡፡
የጎበዝ ነባቢት ነፍሱ
የሰው መዝርዕቱእ አርያ፤ የማይታጠፍ መንፈሱ
በጥራት የታጠፈለትየምድር አጥናፍና አድማሱ፡፡
የየብስ የአየሩ ነበልባል
የማራቶን እፁብ አይጣል፡፡
























የምድር አለሙ ገሞራ
አገሩንበክብር ያስጠራ
ሳተናው እግረ ጆቢራ
ሎጋ ቢቂላ ዋቅጂራ፤
የጎበዛዝ ንጥረ ወዙ
የተስፋ ብርሃን መቅረዙ፤
ስሙን ላገር ስም ሰይሞ፡ የምስራች ያስደወለ
ስንቱን ስንቱን ልበ ሙሉ፡ ከአድማስ አድማስ ያስከተለ፡፡
የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ
ያረጋት የኦሎምፒክ አርማ፡፡
























በወገኖቹ ልቦና ቀና ኩራት ያሳደረ
እንደፍላፃ በአክናፉ የአየርን ሰርጥ የሰበረ
የፍስሃዋን አዋጅ ለአለም በአቅመ ወዙ ያስነገረ፡፡
በአገር ፍቅር ልቡን ሞልቶ ላቡን ነጥቦ የዋተተ
የአለምን ጀግና በአድናቆት በቅን ቅናት ያስሸፈተ
አልሞተም እንበል እባካችሁ "አበበ እንጂ መቼ ሞተ?"

























**********************************
     ምንጭ:---http://www.eaf.org.et

No comments:

Post a Comment