ከደራሲያን ዓምባ

Monday, September 24, 2012

ከመጽሃፍት ገፆች

ደራስያን በተለያዩ ዘመናትና ሁኔታዎች ውስጥ ያጋጠማቸውን የማኅበረሰቡን የሮሮም ሆነ የፍስሐ መንፈስ በመገምገምና አስመስለው በመቅረጽ ሥነ ቃልን ይጠቀማሉ፡፡ ለመልዕክቶቻቸው ማጉያ በማድረግ በሚፈጥሯቸው ገፀ ባሕርያት አማካይነት በልዩ ልዩ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻቸው ውስጥ ሲጠቅሷቸውም እናስተውላለን፡፡


"እግዚአብሔር ሲፈጥረኝ ጥንቱን በዚህ መሬት፣
ሳለቅስ ተወልጄ ሳለቅስ ኖሬበት፣
ሳለቅስ እንድሔድ ወደ ማልቀርበት፣
መከራን ጠግቤ ደስታን ምራብበት፣
ሌሎች የበሉትን እዳ ልከፍልበት፡፡ "


(ከ ፍቅር እስከ መቃብር)

Wednesday, September 19, 2012

የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር

በዘመነ ኢህአዲግ













የዜግነት ክብር በኢትዮጵያችን ፀንቶ
ታየ ህዝባዊነት ዳር እስከዳር በርቶ
ለሰላም ለፍትህ ለህዝቦች ነፃነት
በእኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት
መሰረተ ፅኑ ሰብዕናን ያልሻርን
ህዝቦች ነን ለስራ በስራ የኖርን
ድንቅ የባህል መድረክ ያኩሪ ቅርስ ባለቤት
የተፈጥሮ ፀጋ የጀግና ህዝብ እናት
እንጠብቅሻለን አለብን አደራ
ኢትዮጵያችን ኑሪ እኛም ባንቺ እንኩራ።
*****************************
በ1984 ዓ.ም
ግጥም፦-ደረጀ መላኩ መንገሻ፤
ዜማ፦- ሰሎሞን ሉሉ ምትኩ

*********************
*********************

በዘመነ ደርግ



















ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -ኢትዮጵያ ቅደሚ
በኅብረተሰባዊነት - አብቢ ለምልሚ!
ቃል ኪዳን ገብተዋል - ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ - ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት - ለነፃነትሽ
መስዋዕት ሊሆኑ - ለክብር ለዝናሽ!
ተራመጂ ወደፊት - በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለሥራ - ላገር ብልጽግና!
የጀግኖች እናት ነሽ -  በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ - ለዘላለም ኑሪ።
*************************
በ1968 ዓ.ም 
ግጥም፦-በአሰፋ ገብረማርያም
ዜማ፦-አቶ ዳንኤል ዮሐንስ

*********************
*********************

በንጉሱ ዘመን


ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ
በአምላክሽ ኃይል በንጉስሽ
ተባብረዋልና አርበኞችሽ
አይነካም ከቶ ነፃነትሽ
ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ
አትፈሪም ከጠላቶችሽ።
ድል አድራጊው ንጉሣችን
ይኑርልን ለክብራችን።
****************
በ1919 ዓ.ም
ግጥም፦-በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
ዜማ፦-ኬቨርክ ናልባልድያን

********************

ኢትዮጵያ



ኢትዮጵያ ~ Ethiopia  /aityoP'ya/


ኢትዮጵያ የሚለው ስያሜ መሠረቱ ግሪክ ሲሆን ከክርስቶስ ልደት በፊት በውል ከታወቀችው ከግብፅ በስተደቡብ የሚገኘው የአፍሪቃ ክፍልና ደቡብ ምዕራብ እስያ የሚጠሩበት አጠቃላይ ስም ነበር፡፡ ይሁንና ከክርስቶስ ልደት በኋላ አገባቡ ጠበብ እያለ አሁን ኢትዮጵያ የምትገኝበት አካባቢ መጠሪያ ለመሆን በቃ፡፡ ስያሜውን ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ በጠበበና እስካሁንም ቋሚ በሆነ መልኩ የምናገኘው
በ4ኛው ምእተ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የክርስትናን እምነት የተቀበለው የአክሱም ንጉሥ ዔዛና በድንጋይ ላይ ባስቀረፀው አንድ ጽሑፍ ላይ ራሱን የኢትዮጵያ ንጉሥ ብሎ ሲጠራ ነው፡፡ ከዚያም በተከታታዮቹ ምእተ ዓመታት በጊዜው በተጻፉ ጽሑፎች አክሱም የኢትዮጵያውያን ከተማ፣ አፄ ካሌብ ደግሞ የኢትዮጵያውያንንጉሥ ተብለው ሲጠቀሱ ስናይ ስያሜው ቋሚ መልኩን እየያዘ መምጣቱን እንረዳለን፡፡ በ14ኛው ምእት ዓመት መጀመሪያ ላይ የተጻፈው ክብረ ነገሥት የተሰኘው ንግሥተ ሳባ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ያደረገችውን ጉዞ የሚያትተው መጽሐፍም፣ ኢትዮጵያ የሚለው ስያሜ በአሁኒቱ ኢትዮጵያ ካለችበት ግዛት ጋር ያለውን መያያዝ ኦፊሲዬል አድርጎታል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ነገሥታት መደበኛ መጠሪያቸውም "ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ወይም "ንጉሠ ኢትዮጵያ" ሆኖ ቆይቷል፡፡
 
 

ስለ ኢትዮጵያ ዕይታ

ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ የአፍሪካ ቀንድ በመባል በሚታወቀው አካባቢ የምትገኝ ከአፍሪካ በቆዳ ስፋቷ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ የምትገኘ አገር ናት፡፡ ዙሪያዋን አምስት አገሮች ያዋስኗታል፡፡ በምስራቅ በኩል ጅቡቲና ሶማሊያ፤ በሰሜንና በሰሜን ምስራቅ ኤርትራ፤ በደቡብ ኬንያ እና በምእራብ ሱዳን ናቸው፡፡ ጠቅላላ የቆዳ ሰፋት 1.1 ሚሊዬን ካሬ ሲሆን በውስጧ 7000 ኪ.ሜ የሚደርስ ርዝማኔ ያላቸው አስር ትላልቅ ወንዞችና ወደ 7000 ካሬ ጠቅላላ ስፋት ያላቸው ሀይቆች አሏት፡፡
መልክአ ምድር
ኢትዮጵያ በውስጧ የተለያዩ መልክአ ምድር ያላት አገር ከመሆኗ በተጨማሪ የአየር ንብረት አፈር የእንስሳትና የዕፅዋት ስብጥር የሚስተዋልባት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ በጣም ከፍተኛ የሆኑ ተራሮች ከላያቸው ጠፍጣፋ የሆኑ አምባ የሚባሉ ኘላቶዎች ስምጥ የሆኑ ሸለቆዎች፤ ጥልቅ የወንዝ ሸለቆዎችና ሰፋፊ ሜዳዎች በውስጧ ይዛለች፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 4620 ሜትር ከሚደርሰው ዳሽን ተራራ እስከ 148 ሜትር ከባህር ጠለል በታች እስከሆነው የዳሎል ዲኘረሽን ድረስ የሚሆን ልዩነት ያለው የከፍታና ዝቅታን የምታስተናግድ አገር ናት፡፡
ለም ከሆኑ መሬቶችና ተራሮች ምንም የማይታይባቸው ከሚመስሉ መሬቶች አንስቶ፣ ኢትዮጵያ በብዙ ገባሮችና ትላልቅ እንደ አባይ ተከዜ አዋሽ ኦሞ ዋቢ ሸበሌና ባሮ-አካቦ በመሳሰሉ ወንዞች የታደለች አገር ናት፡፡
ከሜዲትራንያን ምስራቃዊ መጨረሻ ተነስቶ፣ ደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው ሞዛንቢክ ድረስ የሚደርሰው ታላቁ የስምጥ ሸለቆ ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍሏት ያልፋል፡፡
የአየር ንብረት
ኢትዮጵያ እንደ መልክአ ምድራዊ አቀማመጧ የአየር ንብረቷም በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ሁኔታ ይታዩባታል፡፡ የመካከለኛው ኘላቶ አካባቢ ብዙም የማይፈራረቅ አይነት ወይናደጋማ አይነት የአየር ንብረት ይታይበታል፡፡ ዝቅተኛው የአየር ንብረት በአማካኝ 60c ሲሆን ነገር ግን ወደ ቀይባህር በረሀ አካባቢ 600c የሚደርስበት ጊዜዎች አሉ፡፡ በብዙ የአገሪቱ አካባቢ በክረምት ወራት ይኸውም ሰኔ ሀምሌና ነሀሴ ውስጥ ከፍተኛ የዝናብ መጠን ይመዘገባል፡፡ 
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር
የኢትዮጵያ (እንዲሁም በኤርትራ አብያተ ክርስትያናት) ዋና ካሌንደር ነው። አዲስ ዓመት በጁሊያን ካሌንደር አቆጣጠር በኦገስት 29 ወይም 30 የሚጀምር ሲሆን በግሪጎሪያን ካሌንደር ደግሞ 1901 ... እስከ 2099 ... ድረስ በሴፕቴምበር 11 ወይም 12 ይጀምራል። በየአራት ዓመቱ አንድ ቀን ይጨመራል። በአንድ ዓመት ውስጥ አስራ-ሁለት ባለሠላሣ ቀናት እና አንድ ባለ አምስት (ስድስት በአራት ዓመት አንዴ) ቀናት ያሉባቸው ወራት አሉ።
የአመተ ምህረት ዘመናት ከጎርጎርዮስ 'አኖ ዶሚኒ' 7 ወይም 8 አመታት የሚለይበት ምክንያት፣ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 400 አመት ያህል በኋላ አኒያኖስ እስክንድራዊ ዘመኑን ሲቆጥረው ትስብዕቱ በመጋቢት 29 1 .. እንደ ሆነ ስለ ገመተ ይህ ትስብዕት ዘመን 1 አመት ሆኗል። ይህ አቆጣጠር በምሥራቅ ክርስቲያን አገራት ከተቀበለ በኋላም 443 .. ከሮማ ፓፓና ከምሥራቅ አቡናዎች መካከል ልዩነት ደርሶባቸው፤ 517 ሌላ መነኩሴ ዲዮኒሲዮስ ኤክሲጉዎስ ሌላ አቆጣጠር (አኖ ዶሚኒ) አቀረበ። በሱ ግምት ትስብዕቱ የተከሠተበት ቀን ከአኒያኖስ ግምት በፊት 8 አመታት አስቀደመው። አኖ ዶሚኒ አቆጣጠር በምዕራብ አውሮፓ ላይኛነት በማግኘቱ የትስብእት ዘመን 1 አመተ ምህረት አኖ ዶሚኒ 9 .. ሆነ።
የኢትዮጵያ ዘመን ኣቆጣጠር የጁልያን ዘመን ኣቆጣጠር ኣይደለም።
ወራት
የወራት አቆጣጠር የተወረሰ ቅብጢ ዘመን አቆጣጠር ይህም የወጣ ጥንታዊ ግብጽ ዘመን አቆጣጠር ነው። ሆኖም የወሮች ስሞች ግዕዝ ተለውጠዋል።

ቋንቋ
አራት መሰረታዊ የቋንቋ ቤተሰቦች ሲኖር እነርሱም ኩሺቲክ (Cushitic) ፣ ሴሜቲክ (Sematic) ፣ ኦሜቲክ (Omotic) ፣ ኒሎ ሻሮን (Nilo-Saharan) በመባል ይታወቃሉ።
በግምት 83 የተለያዩ ቋንቋዎችና ከ200 የሚበልጡ የአነጋገር ዘዬዎች በአገሪቱ ይነገራሉ።
አማርኛ የብሄራዊ ቋንቋ ሲሆን የንግድና የስራ መግባብያ ቋንቋዎች አማርኛ እና እንግሊዝኛ ናቸው።
መልክአ ምድር
ኢትዮጵያ በውስጧ የተለያዩ መልክአ ምድር ያላት አገር ከመሆኗ በተጨማሪ የአየር ንብረት አፈር የእንስሳትና የዕፅዋት ስብጥር የሚስተዋልባት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ በጣም ከፍተኛ የሆኑ ተራሮች ከላያቸው ጠፍጣፋ የሆኑ አምባ የሚባሉ ኘላቶዎች ስምጥ የሆኑ ሸለቆዎች፤ ጥልቅ የወንዝ ሸለቆዎችና ሰፋፊ ሜዳዎች በውስጧ ይዛለች፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 4620 ሜትር ከሚደርሰው ዳሽን ተራራ እስከ 148 ሜትር ከባህር ጠለል በታች እስከሆነው የዳሎል ዲኘረሽን ድረስ የሚሆን ልዩነት ያለው የከፍታና ዝቅታን የምታስተናግድ አገር ናት፡፡
ለም ከሆኑ መሬቶችና ተራሮች ምንም የማይታይባቸው ከሚመስሉ መሬቶች አንስቶ፣ ኢትዮጵያ በብዙ ገባሮችና ትላልቅ እንደ አባይ ተከዜ አዋሽ ኦሞ ዋቢ ሸበሌና ባሮ-አካቦ በመሳሰሉ ወንዞች የታደለች አገር ናት፡፡
ከሜዲትራንያን ምስራቃዊ መጨረሻ ተነስቶ፣ ደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው ሞዛንቢክ ድረስ የሚደርሰው ታላቁ የስምጥ ሸለቆ ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍሏት ያልፋል፡፡
የአየር ንብረት
ኢትዮጵያ እንደ መልክአ ምድራዊ አቀማመጧ የአየር ንብረቷም በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ሁኔታ ይታዩባታል፡፡ የመካከለኛው ኘላቶ አካባቢ ብዙም የማይፈራረቅ አይነት ወይናደጋማ አይነት የአየር ንብረት ይታይበታል፡፡ ዝቅተኛው የአየር ንብረት በአማካኝ 60c ሲሆን ነገር ግን ወደ ቀይባህር በረሀ አካባቢ 600c የሚደርስበት ጊዜዎች አሉ፡፡ በብዙ የአገሪቱ አካባቢ በክረምት ወራት ይኸውም ሰኔ ሀምሌና ነሀሴ ውስጥ ከፍተኛ የዝናብ መጠን ይመዘገባል፡፡
በከፍታና በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዐይነት የአየር-ንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነሱም:-
  • ደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግረ ሴ.ግ የማይበልጥ፤
  • ወይናደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል ከ1500 እስከ 2400 ሜትር፣ ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስና፣
  • ቆላ - ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስ አከባቢዎች ናቸው።
ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።
*********************************************************************************
ምንጭ:--http://am.wikipedia.org/// http://www.ethiopia.gov.et


Monday, September 10, 2012

የመልካም ምኞት መግለጫዎች ለአዲስ ዓመት በተለያዩ የዓለም ቋንቋዎች ።






















 መልካም አዲስ ዓመት!!!
Melkam Addis Amet
Happy Ethiopian New Year
*****************************
Arabic: Kul 'am wa antum bikhair
Assyrian: Sheta Brikhta
Azeri: Yeni Iliniz Mubarek!
Balochi: Noki saal mubarrak bibi
Bengali: Shuvo Nabo Barsho
Breton: Bloavezh Mat

Bulgarian: ×åñòèòà Íîâà Ãîäèíà(pronounced "Chestita Nova Godina")
Cambodian: Soursdey Chhnam Tmei
Catalan: FELIÇ ANY NOU
Chakma: Nuo bazzor bekkunore
Chinese: Xin Nian Kuai Le
Corsican: Pace e Salute
Croatian: Sretna Nova godina!
Cymraeg: Blwyddyn Newydd Dda
Czech: Stastný Novy rok (or Stastny Novy rok)
Denish: Godt Nytar
Dhivehi: Ufaaveri Aa Aharakah Edhen
Dutch: GELUKKIG NIEUWJAAR!
Eskimo: Kiortame pivdluaritlo
Esperanto: Felican Novan Jaron
Estonians: Head uut aastat!
English: Wishing you all happy new year!
ኢትዮጵያ: መልካም አዲስ ዓመት!
ኢትዮጵያ: እንኳን ከዘመን ዘመን በሰላም አሸጋገራችሁ!
ኢትዮጵያ: አዲስ ዓመት የሰላም የጤና የብልጽግና ይሁንላሁ!
Ethiopian: MELKAM ADDIS AMET YIHUNELIWO!
Ethiopian/Eritrean Tigrigna:RUHUS HADUSH AMET
Finnish: Onnellista Uutta Vuotta
French: Bonne Annee
Gaelic: Bliadhna mhath ur
Galician: Bo Nadal e Feliz Aninovo
German: Prosit Neujahr
Georgian: GILOTSAVT AKHAL TSELS!
Greek: Kenourios Chronos
Gujarati: Nutan Varshbhinandan
Hawaiian: Hauoli Makahiki Hou
Hebrew: L'Shannah Tovah
Hindi: Naye Varsha Ki Shubhkamanyen
Hong kong: (Cantonese) Sun Leen Fai Lok
Hungarian: Boldog Uj Evet Kivanok
Indonesian: Selamat Tahun Baru
Iranian: Sal -e- no mobarak
Iraqi: Sanah Jadidah
Irish: Bliain nua fe mhaise dhuit
Italian: Felice anno nuovo
Japan:: Akimashite Omedetto Gozaimasu
Kabyle: Asegwas Amegaz
Kannada: Hosa Varushadha Shubhashayagalu
Kisii: SOMWAKA OMOYIA OMUYA
Khasi: Snem Thymmai Basuk Iaphi
Khmer: Sua Sdei tfnam tmei
Korea: Saehae Bock Mani ba deu sei yo!
Kurdish: NEWROZ PIROZBE
Latvian: Laimigo Jauno Gadu!
Lithuanian: Laimingu Naujuju Metu
Laotian: Sabai dee pee mai
Macedonian: Srekjna Nova Godina
Madagascar: Tratry ny taona
Malay: Selamat Tahun Baru
Marathi: Nveen Varshachy Shubhechcha
Malayalam: Puthuvatsara Aashamsakal
Mizo: Kum Thar Chibai
Maltese: Is-Sena t-Tajba
Nepal: Nawa Barsha ko Shuvakamana
Norwegian: Godt Nyttar
Oriya: Nua Barshara Subhechha
Papua New Guinea: Nupela yia i go long yu
Pampango (Philippines): Masaganang Bayung Banua
Pashto: Nawai Kall Mo Mubarak Shah
Persian: Sal -e- no mobarak
Philippines: Manigong Bagong Taon!
Polish: Szczesliwego Nowego Roku
Portuguese: Feliz Ano Novo
Punjabi: Nave sal di mubarak
Romanian: AN NOU FERICIT
Russian: S Novim Godom
Samoa: Manuia le Tausaga Fou
Serbo-Croatian: Sretna nova godina
Sindhi: Nayou Saal Mubbarak Hoje
Singhalese: Subha Aluth Awrudhak Vewa
Siraiki: Nawan Saal Shala Mubarak Theevay
Slovak: Stastny Novy rok
Slovenian: sreèno novo leto
Somali: Iyo Sanad Cusub Oo Fiican!
Spanish: Feliz Ano ~Nuevo
Swahili: Heri Za Mwaka Mpyaº
Swedish: GOTT NYTT AR! /Gott nytt ar!
Sudanese: Warsa Enggal
Tamil: Eniya Puthandu Nalvazhthukkal
Tibetian: Losar Tashi Delek
Telegu: Noothana samvatsara shubhakankshalu
Thai: Sawadee Pee Mai
Turkish: Yeni Yiliniz Kutlu Olsun
Ukrainian: Shchastlyvoho Novoho Roku
Urdu: Naya Saal Mubbarak Ho
Uzbek: Yangi Yil Bilan
Vietnamese: Chuc Mung Tan Nien
Welsh: Blwyddyn Newydd Dda!

Wish all your near and dear ones in their country’s language and spread the happiness. Hope you enjoyed reading the Happy New Year in different languages and wishing you all prosperous New Year.
 

መልካም አዲስ ዓመት!!!


Friday, September 7, 2012

እንቁጣጣሽ!!!

 

እንቁጣጣሽ!!!

መስከረም 1

ዘመን መለወጫ

ርእሰ ዓውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ 

****************************************************************************

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ 

 ዓመታት ተፈጽመው አዲስ ዓመት ስንጀምር ቅዱስ ዮሐንስ፣ ዓውደ ዓመት፣ አዲስ ዓመት ፣ እንቁጣጣሽ እየተባለ ይጠራል፡፡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንደሚያስረዱት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይመ ጥንተ ታሪክ በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኃ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት «ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ» ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ ሁለተኛው የሀገራችን ንግሥት ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ዜና ጥበብ እየሰማች ስታደንቅ ትኖር ነበር፡፡ በጆሮዋ የሰማችውን በዓይኗ ዓይታ ለመረዳት ስለፈለገች በግመሎች ላይ ሽቱና እጅግ ብዙ ወርቅ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኝ በኢየሩሳሌም የማይገኝ ልዩ ልዩ ገጸ በረከት አስጭና ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ገባች፡፡ ከንጉሡ ሰሎሞንም ጋር ተገናኝታ የያዘችውን ገጸ በረከት ከሰጠችው በኋላ ብዙ ነገሮችን ጠየቀችው፡፡ እርሱም አንድ ነገር ላይ ሰውሮ ሁሉንም ገለጸላት፡፡ ቤተ መንግሥቱንም በቤተ መንግሥቱ የሚገኙ እጅግ በጣም የከበሩ ዕቃዎችን ሁሉ አስጎበኛት፡፡ ሲያበቃ «ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንልሽ» ሲል እጅግ በጣም የከበረ ዕንቁ አበረከተላት/ሰጣት/፡፡ ወሩም ወረኃ መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው መጥቷል፡፡ አሁን ከሚፈጸመው ሥነ ሥርዓት ደርሶ በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ የሚከበረውም መስከረም አንድ ቀን ነው፡፡ አንድም «ዕንቁ ዕፅ አወጣሸ» ብሎ የአበባውን መፈንዳትን ያስረዳናል፡፡

መስከረም አንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ያጠመቀው የቅዱስ ዮሐንስ መታሰቢያ ዕለትም ነው፡፡ መስከረም ሁለት ደግሞ ይህ አባት አንገቱን የተቆረጠበት ቀን ነው፡፡

በገሊላ ሀገር የነገሠ ሄሮድስ የሚባል ሰው ነበር፡፡ እርሱም የወንድሙን የፊልጶስ ሚስት ሄሮድያዳን ስላገባ ቅዱስ ዮሐንስ ሳይፈራ ንጉሡን «የወንድምህን ሚስት ልታገባት አልተፈቀደልህም» ብሎ ይነግረው ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት ንጉሡ ተቆጥቶ ዮሐንስን አስሮት ነበር፡፡ ሊገድለውም ፈልጐ ሕዝቡ ዮሐንስን በጣም ስለሚወዱት እነርሱን ፈርቶ ተወው፡፡ 

አንድ ቀን የሄሮድስ የልደቱ ቀን በሆነ ጊዜ ታላቅ ድግስ ተደግሶ እንግዶች ተጋባዦች ተሰብስበው ሲበሉና ሲጠጡ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ገብታ ለንጉሡ ዘፈነችለት ደስም አሰኘችው፡፡ ስለዚህ የምትለምነውን ሁሉ ሊሰጣት ማለላት፡፡ እርሷም እናቷን አማክራ የመጥምቁ የዮሐንስን ራስ አሁን በስሀን ስጠኝ አለችው፡፡ ንጉሡም ወታደሮቹን ልኮ በእስር ቤት ሳለ የዮሐንስን ራስ አስቈረጠው፡፡ ራሱንም በሰሀን አምጥተው ለዚያች ልጅ ሰጡአት እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠቻት፡፡ እግዚአብሔርም ለቅዱስ ዮሐንስ አንገት ክንፍ ሰጣት እየበረረችም ለ15 ዓመት አስተማረች፡፡ 

መልካም አዲስ አመት ተመኝተን መጪዉን አመት ጠንክረን የምንሰራበት፣ የጀመርነዉ ነገር ካለ የተሻለ ደረጃ የምናደርስበት፣ የጀመርነዉ ከሌለ ያሰብነዉን የምንጀመርንበት፣ ያሰብነዉ ነገር ከሌለ ደግሞ ለማሰብ የምንነቃቃበት እንዲሆን እንመኛለን፡፡ እንዲሁም ከቻልን ለሰዎች የምንተርፈበት ካልቻልን ደግሞ እራሳችንን የምንችልበት እንዲሆንልን ምኞታችን ነዉ፡፡

 


እንቁጣጣሽ በያመቱ ያምጣሽ!
መልካም አዲስ አመት!

Happy Ethiopian New year!

መጭው አመት የሰላም እና የደስታ
                                    ዘመን ይሁንላችሁ!!!
                 2005 ዓመተ ምህረት